Monday, March 31, 2014

ፖሊሱ ሚኒባሷን በጥይት መታት፤ አንዲት እህት ወዲያው ሞተች ሁለቱ ቆሰሉ


የህዝብን ደህንነት እንዲጠብቁ የሰለጠኑ ፖሊሶች የንፁሀንን ህይወት በማጥፋት ስራ ላይ ተጠምደዋል
news
ትላንትና ማታ ከእምድብር ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ሚኒባስ በአካባቢው የጥበቃ ተረኛ በነበረ ፖሊስ በጥይት ከተመታ በኋላ በውስጡ ከነበሩ ተሳፋሪዎች መሀከል የአንድ ከአረብ ሀገር ተመላሽ እህታችን ህይወት ወዲያው ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ተከስቷል ይላል ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ።
እንደደረሰው መረጃ ከሆነ ፖሊሱ ይህን እርምጃ የወሰደው ሚኒባሱ ኮንትሮባንድ የጫነ መኪና መስሎት እንደሆነ በአካባቢ የነበሩ የአይን እማዬች ቢገልጹም የጥበቃ ፖሊሱ ይህን እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ወደ ላይ ተኩሶ መኪናውን ለማስቆም ወይም ለማስጠንቀቅ ያደረገው ጥረት አለመኖሩን አክለው ይገልፃሉ።
አደጋው የደረሰው በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ ልዩ ስሙ ጋሶሬ እየተባለ በሚጠራው መንደር ሲሆን በቅርብ ጊዜ ይህ አካባቢ ከወልቂጤ ከተማ ተካሏል) የእምድብር ከተማ ነዋሪ የሆነችው ሟች ኮከቤ አለማየሁ ባለ ትዳር እና የሁለት ልጆች እናት ስትሆን በቅርብ ጊዜ ከአረብ ሀገር ተመልሳ ኑሮዋን ለማቸነፍ አነስተኛ ሱቅ ለመክፈት ለሱቅ እሚሆን እቃ ለማምጣት ወደ አዲስ አበባ እየተጓዘች በነበረበት ጊዜ ነው የለፋችለት ትዳሯን እና መስዋዕት የከፈለችላቸውን ልጆቿን ለሚያሳጣት ጥይት በፖሊሱ የተላከባት። አስክሬኑ ለምርመራ ወደ አዲስ አበባ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግስት በታጠቁ ፖሊሶች ህይወታቸው እየተነጠቁ ያሉ ምስኪን ዜጎች ቁጥር በሀገራችን እየጨመረ ይገኛል።
ለሟች ቤተሰቦች ሀዘኑ መራራ ቢሆንም መጽናናትን ለቆሰሉ ቁስላቹ የውሻ ቁስል ይሁንላቹ የሚሉት የዚህ ዘገባ አጠናቃሪዎች “የንፁሀንን ደም ለማጥፋት የሰለጠኑ የሚመስሉትን ፖሊሶችን እያሰለጠኑ ለሚያወጡ ማሰልጠኛዎች እባካችሁ ምልመላና የስልጠና አሰጣጣችሁን በመቀየር ፖሊስ የንፁሀን ጠባቂ እንጂ ስጋት መሆናቸውን አስቁሙልን” ሲሉ ጥሪያቸውን ያቀርባሉ”"

No comments:

Post a Comment