Thursday, March 20, 2014

ቤተክርስቲያን መምህር ግርማን ፎርጂድ ደብዳቤ በማሰራጨት ወነጀለች


 
Memeher Girma
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ” በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡ “መምህር ግርማ ወንድሙ ከፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል” በሚል መምህር ግርማ እያሰራጩት ያለው ደብዳቤ ከቤተክርስቲያኒቱ ጽህፈት ቤት ተፈርሞ ያልወጣ የማጭበርበር ደብዳቤ ነው ሲል በአባ ገርማ (ሊቀጳጳስ/ዶ/ር) የብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርል ልዩ ጽህፈት ቤት የውጭ ግኙነት ሃላፊ ስም መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተገልጿል።
ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መምህር ግርማ የበተኑትንና በመላው ዓለም ከፓትርያርኩ ተዘዋውሬ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኛል የሚለውን ደብዳቤ ማስተናገዷ የሚያወስ ሲሆን አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የፓትሪያርኩ ልዩ ጽህፈት ቤት የወጣውን ደብዳቤ በማስተናገድ ፍርዱን ለአንባቢ ትተዋለች።
ቀጥሎም ፎርጂዱን ደብዳቤ እንዳትቀበሉት ሲል የወጣውን እና መምህር ግርማ ያሰራጩት የተባለውን ደብዳቤ በተከታታይ ለግንዛቤ አቅርበናቸዋል።
ዘ-ሐበሻ መምህር ግርማን በዚህ ህገወጥ የሆነ ደብዳቤ አሰራጭተዋል በሚል በቀረበባቸው ውንጅላ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገችው ሙከራ ባይሳካም እንዳገኘናቸው ሃሳባቸውን ለማቅረብ እንሞክራለን። ሆኖም ግን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች መምህር ግርማ ነሐሴ 25/2005 ዓ.ም ደብዳቤ ተጽፎልኛል ብለው ደብዳቤውን ከበተኑት ከ7 ወር በኋላ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን ማስተባበሏ ከበስተጀርባው አንድ ጉዳይ ሊኖር እንደሚችል ይናገራሉ።
የመምህር ግርማ ደብዳቤ ፎርጂድ ነው አትቀበሉት ሲል የተጻፈው ደብዳቤ
memeher girma holy sionod
መምህር ግርማ በአቡነ ማቲያስ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኝ ደብዳቤ ተጽፎልኛል ሲሉ የበተኑት ደብዳቤ፦
Memher Girma
Memher Girma

ምንጭ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13698

No comments:

Post a Comment