Monday, December 30, 2013

በአዲስ አበባ የቅርብ ጊዜ የጅምላ መቃብር ተገኘ

December 30, 2013
ሁኔ አቢሲኒያዊ
ነገሩ የተከሰተው አርብ እና ቅዳሜ እለት ነው ከስድት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የጃንሜዳ ጦር ካምፕ(በቀድሞ ስሙ ሦስተኛ ሻለቃ) ግቢ ውስጥ በትንሹ ወደ 6 የሚጠጉ አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተገኝተዋል! አስከሬኖቹ ሊገኙ የቻሉት ለመንገድ ስራ የጦር ካምፑ ግቢ አጥር ወደ ውስጥ ፈርሶ መቆፈር ነበረበት፡፡ በዚህ ሂደት ላይ ነው እንግዲህ በስካቫተር ሲቆፈር በመጀመሪያ ሁለት አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተንከባለሉ፡፡ በዚህ የተደናገጡት ሰራተኞች ለጊዜው ስራቸን ያቋረጡ ሲሆን በበነጋው ቅዳሜ እለት ረፋዱ ላይ በሌላ አቅጣጫ ቁፋሮ ሲያደርጉ በዛም በኩል እዲሁ በብርድ ልብስ የተጠቀለሉ አራት አስከሬኖች በተመሳሳይ ሁኔታ ከአፈሩ ዉስጥ ተገኙ፡፡A mass grave in Addis Ababa, Ethiopia
በዚህ መሃል ከጦር ካምፑ አካባቢ የተወሰኑ መኮንኖችና ከፍተኛ ማዕረግ(ጄነራሎች)በትከሻቸው ላይ ያለባቸው ሰዎች ወደ ቦታው በመምጣት ስራው እንዲቆም ትእዛዝ ያስተላለፉ ሲሆን በአካባቢው የነበረውንም ሰው ከቦታው አባረው በትነዋል፡፡ በስፋራው ተገኝተው ሁኔታውን ሲከታተሉ እና በስራው ላይም ተሳታፊ የነበሩ ለሰማያዊ ፓርቲ ቅርብ የነበሩ ሰዎች ፎቶ ለማንሳት ጥረት ቢያደርጉም በወታደሮቹ ተመናጭቀዉ ክልከላ ደርሶባቸዋል፡፡ እንደምንጮቻችን እና የምስል ማስረጃዎች ከሆነ አስከሬኖቹ የተጠቀለሉበት ብርድልብስ አንዳችም ሳይቀደድና ሳይበሰብስ ከነአዲስነቱ መገኘቱ ጅምላ ግድያው በቅርቡ የተፈፀመ ሊሆን እንደሚችል ከፍተኛ ጥርጣሬን አሳድሯል! በጉዳዩ ላይ ማጣራት ለማድረግ ሙከራ ያደረጉት የሰማያዊ ፓርቲ አባሎችንም ፊት

በጀግኖች አባቶቻችን ደም የተቦካው ሉአላዊ ግዛታችን ላይ የሚደረገውን ስውር ሴራ ያለማወላወል በፅናት እንታገለዋለን (ሰማያዊ ፓርቲ)

December 30, 2013
ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ታኅሣሥ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. (December 30, 2013)

የኢትዮጵያንና የሱዳንን ድንበር የማካለሉ ሥራ ከመስከረም 29 ቀን 2002 ዓ.ም. (October 9, 2009) ጀምሮ እየተከናወነ እንደሆነ፣ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚታተመው ዕለታዊ የሱዳን ጋዜጣ ሱዳን ትሪቢውን (Sudan Tribune) በመስከረም 8 ቀን 2002 ዓ.ም. (September 18, 2009) መዘገቡ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያና የሱዳን የድንበር ጉዳይ ያንገበገባቸው ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥና በውጪ የሚኖሩት ዜጎቻችንም ራሳቸውን በተለያዩ “ኮሚቴዎች” እና “ግብረ ሃይሎች” በማደራጀት ለጉዳዩ ክፈተኛ ትኩረት እንዲሰጠው ሲጥሩ ቆይተዋል፡፡ ፓርቲያችን (ሰማያዊ)፣ ለነዚህ ሀገር ወዳድ ዜጎች ያለውን ከፍተኛ አክብሮት ለመግለጽ ይወዳል፡፡Statement from Semayawi party of Ethiopia, regarding Nile issue.
ሆኖም፣ የነዚህን ሀገር ወዳድ ዜጎችና አፍቃሪ-ኢትዮጵያውያን ጥሪና መግለጫዎች ከቁብም ካለመቁጠር፣ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ-ኢህአዲግ መንግሥት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ሥውር የሥልጣን ማራዘሚያ ደባዎችን እየሸረበ እንደሚገኝ አጋልጠዋል። ወያኔ ራሱ ያቋቋመው “የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር ኮሚቴ” አባላት ራሳቸው በተለያዩ ቃለ-ምልልሶች እንዳጋለጡት፣ ወያኔ በአባቶቻችን ደም ተላቁጦ ለተቦካውና የበርካታ ሰማዕታትን ህይወት ላስከፈለው የኢትዮጵያ ድንበርና የግዛት ሉዓላዊነት ግዴለሽነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡ የኢትዮጵያንም ሉዓላዊ ግዛትና ድንበር “በጫካ ውሎችና ስምምነቶች” እያመካኘ ለኢትዮጵያና

Global Poverty and Post-colonial “Development Agendas”: Ethiopia and the West

December 28, 2013
by Paul O’Keeffe
When one thinks of the word ’agenda’ a few obvious  meanings may come to mind – a list of things to do, a plan for a meeting, a goal to achieve or perhaps even an ideology. In the context of international development aid an agenda often means something altogether very different  – a plan or goal that guides someone’s behaviour and is often not explicitly stated. Development aid agendas do not always reflect the needs and desires of the people they propose to serve. More often than not development agendas serve those who institute and organise them. Be it international development donors or governments who receive billions in aid subsidies, development aid and assistance is hardly ever free from condition or expectation on either the donor or receiver side.Ethiopia officially known as the Federal Democratic Republic of Ethiopia
The world of international aid is a multi-trillion dollar exercise with transactions affecting every country on earth. Some give, some receive, some give and receive, but all are involved in aid flows that are ultimately held up as virtuous considerations of man to fellow man. The world has long been used to the cycles of dependency and desperation that these aid flows illustrate. Ethiopia, for example, with its frequent food insecurity issues and prominence as a major receiver of international aid is perhaps the most perfect example of aid desperation and dependency. In 2011 alone Ethiopia received $3.6 billion in Overseas Development Aid (ODA)[1] . This enormous figure represents over half of the Ethiopian regime’s annual revenue. With the international community’s growing concerns for security and economic interests in the Horn of Africa it is not difficult to imagine how this ODA necessitates a certain amount of condition or expectation for the Ethiopian regime. It is, after all, somewhat unrealistic to expect international donors to hand over vast amounts of money to a regime

2013: The Year of Ethiopia’s Rising Cheetahs in Review

December 29, 2013
by Alemayehu G. Mariam*
In January 2013, I proclaimed, “2013 shall be the Year of Ethiopia’s Cheetah Generation.” I promised “to make my full contribution to uplift and support Ethiopia’s youth and to challenge them to rise up to newer heights.” They rose to greater heights. I pledged to “reach out to them, teach them and preach to them”. I feel proud that I was able to deliver on my promise. In December 2013, I was delighted and immensely gratified to stand with Yilikal Getnet, Chairman of Ethiopia’s Semayawi (Blue) Party in Arlington, VA and show my solidarity with Ethiopia’s Cheetah Generation (young people).Semayawi (Blue) Party led thousands of young protesters in Ethiopia
In 2013, the Chee-Hippo Generation made itself known. I declared, “I am damn proud to be a Chee-Hippo”. There is a need to “invent” a new generation, the Chee-Hippo Generation. A Chee-Hippo is a Hippo (older generation) who thinks, behaves and acts like a Cheetah. A Chee-Hippo is also a cheetah who understands the limitations of Hippos yet is willing to work with them in common cause for a common purpose. Chee-Hippos are bridge builders. They build strong intergenerational bridges that connect the young with the old. They build bridges to connect people seeking democracy, freedom and human rights. They build bridges across ethnic canyons and connect people stranded on

Friday, December 27, 2013

ልጓሙን የበጠሰው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የስድብ ፈረስ

December 27, 2013
ከዳኛቸው ቢያድግልኝ
ፕሮፌሰሩ በጽሁፎቻቸው እንዲህ ብለውናል
“…በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው……”  http://www.goolgule.com/abesha-and-begging-1/
             “…አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም፤ ሁሉንም ነገር ብላ ከተከለከለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል፤ በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም፤ አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤ እግዚአብሄር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምናልባትም በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል …….” (ሰረዝ የተጨመረ)
                 እስከናካቴው “ሆድ” የሚባል ቃል ከአበሻ ቋንቋ ፈጽሞ ቢሰረዝ ቋንቋው ብቻ ሳይሆን አበሻም ጉድ ይፈላበታል።  አዕምሮ ፣ ሕሊና የሚባሉትን ቃላት አበሻ አያውቃቸውም፤ ተግባራቸውንም ሁሉ ለሆድ ሰጥቶታል።   (ሰረዝ የተጨመረ) http://www.zehabesha.com/amharic/archives/9015
ልጻፍ ልተው… ምናልባት… እንዲያው ምናልባት በዚሁ የሚያበቁ ከሆኑ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ይሻል ይሆናል ስል ልጓሙን የበጠሰው የስድብ ፈረሳቸው በማንአለብኝነት ጋለበብን። ባእዳን አበሽ እያሉና እየሰደቡ ይገድሉናል። የራሳቸው ታሪክ በረሀብ ቸነፈርና ስደት የተሞላ እንዳልሆነ ሁሉ በመዝገበቃላታቸው ውስጥ ኢትዮጵያን የረሀብ ምልክት አድረገው የሚያዋርዱን በርካታዎች ናቸው። ፕሮፌሰሩ በአንድ ወቅት ሲሉ እንደሰማሁዋቸው  ወያኔዎች ከዱር ወደከተማ ሲገቡ ህዝቡን ፈሪ ለማድረግና የሚያከብረው ምልክት ለማሳጣት በየቀዬው በህብረተሰቡ ዘንድ የሚከበሩትን እያፈላለጉ በአደባባይ ፂማቸውን ይዘው በመጎተት ያዋርዱዋቸው ነበር። ይህን መሰሉ የወያኔዎች ተግባር በሚያሳዝን ሁኔታ በፕሮፌሰሩም ላይ በተደጋጋሚ ደርሶባቸዋል። የወያኔዎች ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን የማዋረድ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ታዲያ ይህ ባለበት ሁኔታ የእውቀት ጣርያ ላይ ደርሰዋል የሚባሉት አዛውንቱ ፕሮፌሰር መስፍንም  በአሮጌና ያለአግባብ በተደረደረ ምሳሌ ይህን መከራ የበዛበትን ህዝባችንን በሚሸነቁጥ የጅምላ ስድብ መቀጥቀጣቸው ግር የሚያሰኝ ሆነብኝ። ይህ ወቅትና ሁኔታን ያላገናዘበ መፍትሄ የመጠቆም፣ የማስተማር አቅምም የሌለው ኢትዮጵያዊነትን የሚያዋርድ ጅምላ ስድብና ሽሙጥ በተከታታይ ሲወርድብን አይቶ እንዳላየ ማለፉ ክብራችንን ለማጉደፍና ለማዋረድ ኢትዮጵያችንን ለማንቋሸሽ ለሚተጉት ዱላ ማቀበል ይሆናል። እናም ይህ ጥያቄ ይከነክነኝ ገባ። እውን አበሻ ሥራ ጠል፣ ለማኝና ሆዳም ነውን? በምን ጥናት በማንስ ትንታኔ?
Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopher
እድሜአቸውን ሙሉ ሀገራችንን አገልግለዋል ሲባል መስማቴ ብቻ ሳይሆን በባህላችን አዛውንት ይከበራልና  ክብራቸውን የሚያጎድፍ  ትችት ማቅረብ አልፈልግም።  ቢሆንም ታድያ የሰሞኑ ማቆሚያ ያጣው የስድብ ጅራፍ ዘላቂ ጉዳቱ ከፍተኛ ነውና

Mentally disabled Ethiopian housemaid faces beheading in Saudi Arabia

December 26, 2013
The Horn Times Newsletter December 26, 2013
by Getahune Bekele-South Africa

In the first place, the charge was motivated by conjugation of hate and barbarity common in Saudi Arabia. Unable to disavow the accusation labeled against her without a lawyer or even an interpreter, with her hair disheveled and her face hoary with terror, eyes darting from one corner to the other, the Ethiopian woman stood before three heavily bearded Islamic judges silent and motion less.The absolutist monarchy of Saudi Arabia
She does not remember her own name and no one knows for how long she has been subjected to severe abuse by her Saudi employers. No passport or travel document was found in her possessions. The Horn Times is still trying to establish her real name and family address back home in Ethiopia.
Despite the great discrepancy between the police and her employer’s version of the incident, the 26-year-old mentally disabled woman was sentenced to death on Tuesday 24 December 2013, in the

Thursday, December 26, 2013

ለኢትዮጵያ ሰማያዊ ፓርቲ ምስክርነት

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ሰማያዊ ፓርቲን እንደፖለቲካ ድርጅት/ፓርቲ ለምን እንደምደግፈው፣
እ.ኤ.አ ዴሴምበር 15/2013 ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብላ በምትገኘው አርሊንግተን ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተዘጋጀው የሰማያዊ ፓርቲ የመጀመሪያ ስብሰባ ላይ ተገኝቼ  ንግግር እስካደረግሁባት ዕለት ድረስ በበርካታ ጥያቄዎች እወጠር ነበር፡፡ አንደኛው ተደጋግሞ የሚጠየቀው ጥያቄ ለበርካታ ዓመታት ገለልተኛ ሆኘ እና ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ቡድን ጋር ሳልወግን ከቆየሁ በኋላ በአሁኑ ጊዜ ለሰማያዊ ፓርቲ ለምን ያልተቋረጠ ድጋፍ በመስጠት ላይ እንደምገኝ በሚቀርብ ጥያቄ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡
በኢትዮቱብ ድረገጽ/ethiotube.com በሰጠሁት ቃለ ምልልስ በግልጽ እንዳስቀመጥኩት ለሰማያዊ ፓርቲ ቀጣይነት ያለው ድጋፍ የምሰጥበት ዋና ምክንያት የኢትዮጵያ ትኩስ ወጣት ኃይል የሀገሩን መጻኢ ዕድል የመወሰን እና በሰላማዊ የትግል ሂደት በመሳተፍ ለውጥ ለማምጣት ዝግጁ ነው የሚል ሙሉ እምነት ያለኝ በመሆኑ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ከ35 ዓመት የዕድሜ ክልል በታች የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል 70 በመቶ ይሸፍናል፡፡ እንዲሁም በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ በአብዛኛው የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ሰለባ ሆኖ የሚገኘው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ አብዛኛው የወጣት ህብረተሰብ ክፍል የኢትዮጵያ የማጎሪያ እስር ቤቶች የፖለቲካ ጭቆና እና ማስፈራራት፣ ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር የመዋል እና እስራት፣ የስቃይ፣ የመብት እረገጣ እና ከህግ አግባብ ውጭ የእስር ቤት አያያዝ ሰለባ ዒላማ ሆኖ ይገኛል፡፡ አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስር በሰደደ የስራ አጥነት ወጥመድ ተጠፍረው እና ጥራት ያለው የትምህርት ዕድል እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት መብታቸውን ተነፍገው በሀገራቸው ላይ የበይ ተመልካች ሆነው ይገኛሉ፡፡ እዚህ ላይ የእኔን “አስረጅ” ምሰክርነት ለማስመዝገብ እንዲሁም ለሰማያዊ ፓርቲ ‘ምስክርነት’ ለመስጠት ያህል  በማያወላውል መልኩ የኢትዮጵያ ወጣቶች የቆሸሸውን የጎሳ ፖለቲካ፣ አስፈሪውን የኃይማኖት ጥላቻ  እና በውሸት ድር እና ማግ የተደወረውን የቅጥፈት ተምኔታዊ ፖለቲካ በጣጥሰው በመጣል “ፍቅር የነገሰበት የኢትዮጵያ

ቴዲ አፍሮ እና ጥሬ ጨዎች

December 25, 2013
ሁኔ አቢሲኒያዊ
ፒተርቦሮው ዩ.ኬ

Ethiopian Artist Teddy Afroቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) በብዙዎች ሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ትልቅ ስፍራየሚሰጠው ወጣት ከያኒ ነው፤ በሙዚቃዎቹ በሚያነሳው ሀገራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ታሪካዊና ወቅታዊ ጉዳዮች የተነሳ የብዙዎችን ቀልብ ለመግዛት የቻለ ይመስለኛል፡፡ የእርሱን ታላቅነት መግለፅ የዚህ ጹሑፍ ዓላማ፣ ጥያቄም፣ የማወቅም ፍላጎት አይደለም፡፡
ይልቁንም ለዚህ አጭር መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ ከሰሞኑ በአንዳንድ ጥቃቅን እና አነስተኛ ካድሬዎች እንዲሁም መንግስትን ለምን እንደሚቃወሙ እንኩአን በማያውቁት እንደ እነ ጃዋር መሀመድ የመሳሰሉ ሰሞንኛ ትችታቸውን በመሰንዘራቸውን ምክንያት እኔም የተሰማኝን ልጨምር በሚል ነው፡፡
እንደምናውቀው ቴዎድሮስ ካሣሁን በዚህች የሙዚቃ ህይወቱ ከዛቻ እስከመታሰር ድረስ የደረሰ መሆኑ እሙን ነው ይህም የደረሰበት የተለየ ሰው ስለሆነ ነው
ቴዲ ሺህ ዘመናት ስልጣኔያችንና ታሪካችን፣ ጥበባችን በፍቅር፣ ፍቅራችን በጥበብ የተገመደበት ውሉ ከየት ተጀምሮ የት እንደተቋረጠ ታሪክንእንጠይቅ ዘንድ እንዲህ ሲል በቅኔው ተመራምሮ ያመራምረናል፡-
ብራናው ይነበብ ተዘርግቶ ባትሮኖሱ ላይ፣
የእነ ፋሲለደስ የእነ ተዋናይ፣
የት ጋር እንደሆነ ይታይ የእኛ ጥበብ መሰረቱ…፡፡
እናም እስቲ ታሪክ ይታይ፣ ይመርመር፣ ዘመናትን ያስረጁና የተሻገሩ ብራናዎቻችን ይውጡ፣የሺህ ዘመን የሃይማኖት፣ የጥበብ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔና የፍልስፍና ድርሳኖቻንን ይታዩይመርመሩ… በአክሱም ስልጣኔ፣ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ትንግርት፣ በጎንደርበእነ ፋሲለደስ የስልጣኔ አየር ዝናዋ የናኘላት፣ እነዛ ፍቅርን በጥበብ አስውበው በቅኔያቸውናበማኅሌታቸው ሰማይ ሰማያትን ሰንጥቀው በመንፈሳቸው ጸባዖት የደረሱ፣ በፍቅር ጧፍ የነደዱበማሕሌታዩ ያሬድ መንፈስ የተነሱ እንደ ተዋናይ ያሉ የቅኔ የጥበብ ጉልላቶች እንደ አጥቢያኮከብ በደመቁባት ምድር ዛሬን ፍቅር የተራብን፣ ጥበብን የተራቆትን፣ ስለ ፍቅር

ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ?

December 25, 2013
ማስተዋል ደሳለው
ላለፉት 8 እና ዘጠኝ ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ አያደገ ነው ሲባል እንሰማለን፤  የእድገት ፍጥነቱ  ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄውች  ቢኖሩም መንግስት  የመንገድ ግንባታ ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታወችን እና መሰል ነገሮችን  በመጥቀስ እድገት እንዳለ አስረግጦ ይከራከራል::  በሌላ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ተመዘገበ በሚባልባቸው ዓመታት በዋጋ ንረት የህዝቡ ኑሮ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ  እንደሆነ በግልፅ የሚታይ ነገር ነው:: ታዲያ  የኢኮኖሚ እድገት አለ በተባለባቸው ዓመታት የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ? ይህን ጥያቄ ከ 7 ዓመት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ  ተጠይቀው የሰጡት መልስ የዋጋ ንረቱን የኢኮኖሚ እድገቱ እራሱ የፈጠረው ጉዳይ ነው ነገር ግን ቀስ በቀስ እድገቱ ሲቀጥል ራሱ እድገቱ ችግሩን ይፈታዋል ብለው ነበር፤ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በዃላም እንኩአን ሊሻሻል  የህዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየባሰበት ሂዷል::  ችግሩ የተለያዩ  ምንጮች ቢኖሩትም በዋናነት በ 2 ከፍሎ ማየት ይቻላል::
፩. የኢኮኖሚ እድገቱ ምንጭ
፪. የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር
የኢኮኖሚ እድገት ማለት በአጭሩ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ማለት ነው::  በመጀምሪያ ላለፉት 8  እና ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ  የተፈጠሩት ተጨማሪ ሀብቶች ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ፤  በአብዛኛዉ ሀገሪቱ ዉስጥ የተፈጠሩት ሀብቶች ከመንገድ ፣ ከሕንፃ እና ከ ከኃይል ማመንጫ ከግንባታ ጋር የተያያዙ ናቸው:: በመቀጠልም የዚህ ሀብት የገንዝብ ምንጭ ምንድን ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል፤ የገንዘቡ ምንጭ በዋናነት ከብድር እና እርዳታ የተገኘ ሀብት ነው ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1998 ዓም ጀምሮ በሶማሊያ በመጀመሪያ የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት በመቀጠልም የአልሻባብ እንቅስቃሴ መጠናከር ለኢትዮጵያ ትልቅ ሲሳይ ይዞ ነው የመጣው:: በሶማሊያ ያለዉን ሁኔታ  ለመቆጣጠር ምዕራባዉያኑ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ  በዋና አጋርነት የተሰለፈችዉ ኢትዮጵያ ላለፉት ስምንት ዓመታት በየዓመቱ በቢልየን ዶላር

Tuesday, December 24, 2013

ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን! “ከ 40 ግድብ አንድ የአሰብ ወደብ” – ከሰመረ አለሙ


ኤርትራዉያኖች ተበልጠዉ በኢትዮጵያ ተንደላቅቀዉ የሚኖሩበትን ሁኔታ ከተነጠቁ በሗላ እንደገና እጃቸዉ ለማስገባት በተለያየ ዘዴ ቢጠቀሙም ህዋአት እና ሻቢያ “እባብ ለባብ ይተያያል ካብ ለካብ” አይነት ሆነና ኤርትራዉያን የፈለጉትን ያህል ሳይሆንላቸዉ ቀርቶ እዚሀ ላይ ተደረሷል። የጸሀየ ግብአተ መሬት ፉከራ ከከሸፈ በሗላ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያን ሊበትንልን ይችላል የሚሉትን ሀይል እና ዘዴ ቢበደሩም መላ ቢመቱም ቢያሰባስቡ እና ቢያሰለጥኑም፤ የኢትዮጵያ አንድነት ፍንክች ሳይል ቀርቶ እዚህ ላይ ይገኛል። የኤርትራ ምሁራን ኢትዮጵያ ያስተማረቻቸዉ ተራ ወርደዉ የሚያስገምት ጽሁፍ ቢጽፉም፤ በቀይ ባህር ማተሚያ ቤት የእዉሸት ፋብሪካቸዉ ተረት መሰል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢያሳትሙም፤ ቅጥፈት የተሞላዉ ወረቀት ቢጽፉም ድካማቸዉ ሁሉ ያለምንም ፍሬ ልፋት ብቻ ሁኖ ቀርቷል
ታድያ ለሁሉም ብልሀት አለዉ እንዲሉ ይህ ዘዴ ያለመስራቱን የተረዱ ኤርትራዉያን አቶ መለስንና ለኤርትራ ስስ ልብ ያላቸዉን የህወአት ባለስልጣኖች በመጠቀም ዛሬም ከዜጋዉ በላይ የኢትዮጵያን በረከት እየተጎናጸፉ ይገኛሉ። በተለይ ከአቦይ ስብሀት አለንላችሁ መግለጫ በሗላ ብዙ ኤርትራዉያን ባላቸዉ ንክኪ አማካኝነት በብዛት ወደ ሀገር ጎርፈዋል ከኢትዮጵያ ሳይባረሩ የቀሩትን ወገኖቻቸዉንና በዉጭ ሀገር በሚኖሩ ኤርትራዉያን አማካይነት የዉስጥ ለዉስጥ ግንኙነታቸዉን በማጠናከር ኢትዮጵያ ዉስጥ የቀድሞ ቦታቸዉን ይዘዋል።
በቅርቡ በወጣዉ ጽሁፍ ወደ 1700 የሚሆኑ የኤርትራ ተወላጆች ከኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በላይ ቅድሚያ ተሰጥቷቸዉ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ጎርፈዋል ይህ አፊሲያላዊ ቁጥር ነዉ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ቁጥር እንዳላቸዉ እማኝነት ያላቸዉ ዜጎች በቁጭት ይገልጻሉ። እንግዲህ ልብ ይበሉ እንደ አይን ብሌን በምናያቸዉ የትምህርት ተቋማት ኢትዮጵያዊዉ ወጣት በጫት የቀን ህልም ሲያልም ትላንት ኢትዮጵያ ላይ የተኮሱ ዛሬም ለኢትዮጵያ ክብር እና ፍቅር የሌላቸዉ ኤርትራዉያን በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ሲማሩ በእጂጉ ያሳዝናል።እነሱ እንዲማሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊዉ ቦታዉን ለነሱ መልቀቅ አለበት ማለት ነዉ።
ethiopias-planned-renaissance-damይህ በትምህርት ዘርፍ የተገኘዉ መረጃ ነዉ። በንግድ፤እርሻ፤ፐሮፐርቲን በተመለከተ ከሀገሬዉ ነዋሪ በላይ እዛ ያሉትም ከኤርትራ፤ከአዉሮፓ እና አሚሪካ እየጎረፉም በከፍተኛ ሁኔታ በመጠቀም፤በመጠቃቀም፤ከባንክ በመበደር እና በማምታት ህገ ወጥ ጥቅም በማግኘት ላይ ይገኛሉ። ገንዘብ ማሸጋገር ዋናዉ አገር መጉጃቸዉ ነዉ በዚህም ሂደት ገንዘብ አገሩን እየለቀቀ በባህር ማዶ ባንክ እና በዉጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ላይ ይዉላል። እነሱም በዚህ ህገ ወጥ ስራ አንድም ጠላታቸዉ ኢትዮጵያን ይጎዳሉ አንድም ትርፋቸዉን ያደልባሉ። በህጋዊ መንገድ ቀረጥ ከፍለዉ ከመስራት ይልቅ ህገወጥ የሆነዉ መንገድ ባያተርፋቸዉም ይመርጡታል።
የሚያሳዝነዉና አንጀት የሚያበግነዉ እኛዉ መሀል ስንት ቤት ሰርተሀል? ሰሞኑን ምን ልከሀል? ትንሺ ገንዘብ ሰጥተህ በትግራይ በኩል ዘመድህን አስመጣ እያሉ በድፍረት ሲያወሩ በጣም ልብ ይሰብራል። ይህች ሀገር መች ነዉ ለዜጎቿ የምትሆነዉ? መች ነዉ

ከርዕዮት ዓለሙ ችሎት ጀርባ ያለው ጥቁር ዳኛ ማነው? – የሰነድ ማስረጃ የያዘ ጥብቅ ምስጢር


ከጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ
ክፍል አንድ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር አስር ቀን 2004 ዓ.ም በእነ ርዕዮት አለሙ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኞች በነጻ ህሊና የሰጡት ፍርድ ነው ብሎ ያመነ ሰው አልነበረም፡፡ እዚህም እዚያም ሲወራ የነበረው ውሳኔው በመንግስት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንን ጨምሮ በርካታ ሰወች ይህንኑ በአደባባይ ጽፈውታል፡፡ ቆየት ብሎ ግን ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ የሚገልጹና ተጨማሪ ነገር ለማወቅ የሚገፋፉ መረጃዎች ወደኔ መምጣት ጀመሩ፡፡
እርግጥ የኢትየጵያ የፍትህ ስርአት በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀና ነጻነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት የጥርጣሬ ድምጾች መሰማታቸው በራሱ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምር እንዳስብ የሆንኩት ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ በመስማቴ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በፊት በነበረው የፍርድ ሂደት ያስተዋልኳቸው ሦስት አጠራጣሪ ክስተቶቸ ናቸው እንደ ጋዜጠኛም ሆነ እንደ ርዕዮት የቅርብ ሰው ስለ ጉዳዩ ብዙ ለማወቅ እንድታትር የገፋፋኝ፡፡
የመጀመሪያው፣ ርዕዮት በማዕከላዊ ምርመራ ላይ እያለች የታዘብኩት ነው፡፡ ርዕዮት በተያዘች በማግስቱ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርባ ፖሊስ የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ አባቷና ጠበቃዋ የሆኑት አቶ አለሙ ደግሞ ቤተሰብ እንዲጠይቃትና የህግ ምክር እንድታገኝ አመለከቱ፡፡ ዳኛዋም ፖሊስ ይህንኑ እንዲፈጽም አዘውና የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሰጥተው ችሎቱ አበቃ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ርዕዮት፣ ጠበቃም ሆነ ቤተሰብ ሳታገኝ 28ቱ ቀን አለፈ፡፡
የነበረው አማራጭ የቀጠሮው እለት ጠበቃዋ ገብተው ድጋሜ እንዲያመለክቱ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ እኛም ፍርድ ቤት ስትመጣ ጠብቀን ቢያንስ አይኗን ለማየት ጓጉተናል፡፡ በዕለቱ የሆነው ግን በጣም አስገራሚም አሳዛኝም ነበር፡፡
ቀጠሮው ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ነበረ፡፡ በዚያን ዕለት ጠዋት 2፡30 ቁርስ ላደርስላት ወደ ማዕከላዊ ስሄድ ከዚያን ዕለት በፊትም ሆነ በኋላ አይቻት የማላውቃት አንዲት ልጅ “ርዕዮትን በሌሊት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዋታል ሮጠህ ድረስባት” ብላኝ ካጠገቤ ብን አለች፡፡ ለአቶ አለሙ በስልክ ይህንኑ ነግሬ ወደ ፍርድ ቤቱ አመራሁ፡፡ ቦታው ቅርብ በመሆኑ 10 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ደረስኩ፡፡ እኔ ወደ ግቢው ስገባ ርዕዮት በፒካፕ መኪና ተጭና እየወጣች ነበር፡፡
የፍርድ ቤቱ የቀጠሮ ሰዓት የተለወጠው ባጋጣሚ ወይም በስህተት ሊሆን ይችላል በሚል ይህ ለምን እንደሆነ መዝገብ ቤቱን ጠይቀን የተረዳነው ኬዙን ያየችው ዳኛ በህመም ምክኒያት ለረጅም ጊዜ ስራ የምትገባው ከሰዓት በኋላ ብቻ መሆኑንና ሁኔታው

Monday, December 23, 2013

የኢህአዴግ አዲሱ አሰላለፍ ፪ – ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)


 
samora and azeb
በድህረ-መለስ ኢትዮጵያ የፖለቲካው ሥልጣን በስርዓቱ ልሂቃን መካከል ከሚደረገው የኃይል መተናነቅ አንጻር፣ ዛሬም ከመፈራረቅ ጣጣው የተላቀቀ የማይመስልባቸው ምልክቶች መታየታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአራት ወር በፊት በዚህ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ባቀረብኩት ፅሁፍ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ተፈጥሮ ከነበረው ክፍፍል የትኛው ቡድን የበለጠ ጉልበት አግኝቶ በአሸናፊነት መውጣት እንደቻለ ከገለፅኩ በኋላ ፅሁፉን የቋጨሁት እንዲህ በማለት ነበር፡- ‹‹የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈልግም፡፡››
እነሆ በዚህ ፅሁፍ ደግሞ በቅርቡ በተጨባጭ የታዩትን አዳዲስ ኩነቶች እና ይህንኑ ተከትለው ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የምገምታቸውን ‹የቢሆን ዕድሎች› (Scenarios) ለማየት እሞክራለሁ፡፡
ሰላም የራቀው-ኢህአዴግ
በግንባሩ አባል ድርጅቶች መካከል ዛሬም ድረስ ሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ፖለቲካ አልሰፈነም፤ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ጠቅልሎ ይዞ በነበረው በቀድሞ ሊቀ-መንበሩ ህልፈት ሳቢያ የተፈጠረው የአመራር ክፍተት እና እርሱን ሊተካ የሚችል መሪ ማግኘት ባለመቻሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ከሕግ ይልቅ የጠመንጃ ኃይልና የግለሰብ አምባገነናዊነት በገነነበት ሀገር ‹የማይገመቱ ክስተቶች› (Unpredictable Event) ማምጣታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡
የሆነው ሆኖ በዚህ አጀንዳ ለመመልከት የምሞክረው ጉዳይ፣ በአሁኑ ጊዜ ሀገር እየመራ ያለው ኃይል ለሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ በአንፃራዊነት በጥምር የሚሰራ መሆኑን በማስረገጥ ነው፡፡ የእነዚህ ሁለት ቡድኖች የጉልበት ምንጭም የታጠቀውን ኃይል

የአማራ ዴ/ኃ/ን ለሱዳን ተላልፎ በተሰጠው መሬት ዙሪያ “ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል” የሚል መግለጫ አወጣ


 
Amara Democratic Force
ጋዜጣዊ መግለጫ 
“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!!
ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ
ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦
  1. በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም  በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።
  2. በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር

በሳዑዲ አረቢያ ዛሬ የተነሳው የሸሜሲ መጠለያ ሁከት እልባት ሳያገኝ ቀረ


በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦
የዛሬው የሽሜሲ መጠለያ ሁከት …
የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ” ህጋዊ ሰነድ የማታሟሉ ወደ ሃገር ቤት ግቡ! ” ያወጣውን ተደጋጋሚ መረጃ ተከትሎ ከአምስት ቀናት ጅምሮ ወደ ሽሜሲ መጠለያ በአስር አውቶቡስ በላይ ሆነው የገቡ ኢትዮጵያውያን ሜዳ ላይ ተጥለው ለከፋ መጉላላት መዳረጋቸው ገልጸዋል። አኒሁ ቅሬታ አቅራቢ ዜጎች በማከልም የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዛሬ ጠዋት ሊያነጋግሯቸው የመጡ ቢሆንም ” ተረጋጉ እንመለሳለን !” ብልዋቸው መፍትሄ ሳይሰጧቸው እንደሄዱ ገልጸውልኛል። የሃላፊዎች ሙሉ ቀን መጥፋት ያበሳጫቸው ነዋሪዎች ዛሬ ከቀትር በኋላ በነፍሰ ጡር ፣ በህጻናት ላይ እያደረሰ ያለውን መንገላታት እየጎዳቸው መሆኑን በመግለጽ ለሳውዲ ሃላፊዎችን መፍትሔ ቢጠይቁም ” መፍትሄው በእናንተ ሃላፊዎች እጅ እንጅ ፣ በእኛ እጅ አይደለም! ” በማለት እንደመለሱልቸው እና ነዋሪው በብስጭት አስወጡን በሚል ወደ በሮች ቢጠጋም በወታደሮች መከልከላቸው በምሬት ገልጸውልኛል። ለሶስት ሰአታት በመጠለያው ውስጥ በተከሰተው ተቃውሞ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ወደ ቦታው በመሄድ ነዋሪውን አለማረጋጋታቸውን ብዙዎችን አሳዝኗል ።
(ፎቶ ፋይል)
(ፎቶ ፋይል)

ዛሬ በሽሜሲ መጠለያ የተነሳው ግርግር መንስኤነት በጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች እና በሳውዲ የመጠለያው ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር በተከሰተ አለመግባባት እንደሆነ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረጉት ሙከራ ለመረዳት ችያለሁ! የአለመግባባቱ ምንጭም መኖሪያ ፍቃዳቸውን ጥለው ወደ ሃገር የሚገቡ ዜጎችን ሰነድ ማጓተት ተከትሎ የቆንስል ሃላፊዎች ” ወደ ሃገር መግባት የሚፈልጉ ዜጎቻችን የመውጫ ሰነድ እስካልተሰጠ ድረስ ሰነድ አንሰራም!” አስገዳጅና ጠቃሚ መከራከሪያ በማቅረባቸው እንደሆነ ያሰባሰብኳቸው

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ተጠቃሚ ልትሆን ነው


ቅዳሜ ዕለት የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዘገበው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ልትጠቀም መሆኑን ዘግቧል። ጋዜጣው ጨምሮም ምእመናን ለቤ.ክ ሲሰጡ ደረሰኝ የሚጠይቁበት አሰራር ይኖራል ብሏል።
የአዲስ አድማስ ሙሉ ዘገባ እንደሚከተለው ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽንን ለገቢ መሰብሰቢያነት ለመጠቀም የሚያስችላቸው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑ ተገለጸ፡፡
ዘመኑን ያልዋጀውንና ጥራት የጎደለውን፣ ለሙስናና ብክነት የተጋለጠውን የቤተ ክርስቲያኒቱን የፋይናንስ አሠራርና ቁጥጥር ችግር ግልጽነት፣ ወጥነት፣ ተቀባይነትና ተጠያቂነት ባለው የፋይናንስ አያያዝ ሥርዐት ለመቅረፍና ለማድረቅ ያስችላል፤ በሚል በቀረበው የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ረቂቅ ላይ እንደተጠቀሰው÷ በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገቢ ገንዘብ ሕጋዊ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት የሚገባ ሲኾን ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስትር ማሽን እንደሚከናወን ተመልክቷል፡፡
bole_church_ethiopia-300x225 (1)
የሀ/ስብከቱ አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽን ተጠቃሚ መኾናቸው በገቢ ሒሳብ አሠራርና ቁጥጥር እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመከላከል ያስችላል፡፡ በጥናቱ ላይ በመነሻነት ከተዘረዘሩት ችግሮች ለመረዳት እንደሚቻለው በዕለት ገቢዎችና ደረሰኝ አጠቃቀም ረገድ፡- የቤተ ክርስቲያኒቱን የገንዘብ ገቢ ሰነዶች በሕገ ወጥ መንገድ አሳትሞ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ለግል ገንዘብ ይሰበሰባል፤ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የተከለከለ ደረሰኝ ጥቅም ላይ የሚውልበት አጋጣሚ ታይቷል፤ ከደረሰኙ በበራሪው/ለከፋዩ ከሚሰጠው/ የተለየ መጠን በቀሪው ላይ መጻፍና የግል ጥቅምን ማካበት ይዘወተራል፤ በዘወትርና በክብረ በዓላት በርካታ ገንዘብ ገቢ ቢኾንም በዕለቱ ወደ ባንክ ያለማስገባት ኹኔታ አለ፤ ምእመናን ለሚከፍሉትና ለሚሰጡት ገንዘብ ከመተማመን አንጻር ደረሰኝ

Witness for Ethiopia’s Semayawi (Blue) Party

December 22, 2013
by Alemayehu G. Mariam*
Why I support Semayawi party as a political party
The first Semayawi (Blue) Party town hall meeting in the US
My support for Semayawi Party should be viewed as an expression of my total confidence in the power of Ethiopia’s young people. Prof. Alemayehu G. Mariam
In the days leading up to my speech at the first Semayawi (Blue) Party town hall meeting in Arlington, VA, just outside of Washington, D.C., on December 15, I was peppered with all sorts of questions. The one recurrent question revolved around my unreserved support for Semayawi Party after so many years of staying neutral and unaligned with any Ethiopian political party or group.
As I explained in my interview on ethiotube.com, my support for Semayawi Party should be viewed as an expression of my total confidence in the power of Ethiopia’s young people to change the destiny of their country and their readiness to struggle for peaceful change. The percentage of Ethiopia’s population under the age of 35 today is 70 percent. The vast majority of the victims of human rights violations in Ethiopia today are young people. The targets of political persecution and harassment, arbitrary arrests and detentions, torture, abuse and maltreatment in the prisons are largely

Sunday, December 22, 2013

የተሳካ ትርጉም ያለው – እንቅስቃሴ በሲቢሊቲ ሩም። ሥርጉተ ሥላሴ


ሥርጉተ ሥላሴ 22.12.2013
sreate1ዕለቱ ሰንበት የተቀደሰ የተወደደ በፈጣሪው የተመረጠ ነበር። በዲኔግዲ አማክኝነት ሸገር የዘገበው የታልቅ ሚስጢር ዕውነተኛ ቀን ነበር 08.12.2013። በዚህ ሰዓት ነበር አባ መላ /አቶ ብርኃኑ ዳምጤ/ የሩሙ ባላቤት እጅግ በተመሰጠና ተቆርቆሪነቱ በአዬለ ሁኔታ በዕለቱ ስልኩን ፈልጎ ቃላቸውን በጀሯችን ያደረሰን። ስደት ደስታን የሚገፍ ሲሆን ያን ቀን ግን እውነተኛ ደስታ ነበር የተሰማኝ ከደስታም በላይ ሐሴት። በወቅቱ „ኢትዮጵያዊነት የታላቁን የሰላም አባት የኔልሰን ማንዴላ ህይወት የታደገ ታላቅ ሚስጢር …. አነጠረ።“ በሚል አንድ መታጥፍ ቢጤ ጽፌ ዘኃበሻም ታድጎኝ ለንባብ በቅቶ ነበር አመስግናለሁም።
አባ መላ ጥሩ ተናጋሪ ነው። ንግግር ሥነ – ጥበብ ነው። ጸጋም ነው። ተሰጥዖ። ሥጦታውም የማዳህኒዓለም ቢሆንም በክህሎት፤ በስልጠና ሥነ ደንቦችን በማጥናት ማሳደግ የሚቻል ጉልበታም ፊኖሚና ነው። ንግግር አድማጭን ወደ ተፈለገው አቅጣጫ የሚመራ የተዋጣለት መሪ ነው። ጥሩ ንግግር … በእጅ ያለ ወርቅ ነው። ጥሩ ንግግር ገዢ መሬት ላይ አለ አጥቂ ሰራዊት ነው። ይህን ለመልካም ተግባር ካዋሉት ውስጥ ዕውቅ የዓለማችን ሰዎች ውስጥ ኪንግ ማርቲን ሉተር፤ ፕሬዚዳንት አብርኃም ሊንከን፤ ማህተመ ጋንዲን ትናት፤ ዛሬ ደግሞ ፓኪስታናዊዋ የ16 ዓመቷ ታዳጊ ወጣት የታለቢና ጥቃት ሰለባ ሆና ከሞት የተረፈቸው ማላለ ለምሳሌነት ብናነሳ … ለጥፋት ደግሞ ጀርማናዊ አዶልፍ ሂትለር – ለናኒዝም፤ ሞሶሎኒ – ለፋሺዝም ተግባራዊነት ህዝብን በምዕላት ያንቀሳቀሱበት ታላቅ መሳሪያ ነው።
እኔ የአባ መላን የንግግር ጸጋ የማዬው ከዚህ አንጻር ነው። አባ መላ የተዋጣለት ተናጋሪነቱ ብቻ ሳይሆን የድምጹ ቃና ሳቢነት፤ እንዲሁም ሳቁ እራሱ ውበት አለው። ጥሩ ተናጋሪ ልብን ገዝቶ፤ ግርቶ ወደ ተፈለገው አቅጣጫ የመምራት ሞገዱ ሆነ አቅሙ መጠነ

Explaining the Ethiopian outmigration: Incentives or Constraints?


By Seid Hassan & Minga Negash
Seid Hassan & Minga Negash
Dr. Seid Hassan(right) & Dr. Minga Negash(left)
In both theory and practice, pull and push factors drive migrants out of their own countries of origin. The factors are complex but they are in general categorized as: (a) demand-pull factors, represented by better economic opportunities and jobs in the host (new) country; (b) supply-push factors, represented by the lack of economic opportunities, jobs, and economic downturns, political oppressions, abuses of human rights by home country governments, religious intolerance (constraints), war, conflict and insecurity in the home country; (c) mediating factors that accelerate or constrain migration which may include the existence or prevalence of opportunities available to human smugglers, fly by night recruitment agencies, registered recruitment agencies operating within the legal system and government policies encouraging/incentivizing citizens to migrate; and (d) social network (pull) factors such as the existence of relatives, friends and acquaintances in host

Saturday, December 21, 2013

አድርባይነት (ለጥቅም ሕሊናን መሸጥ)

December 21, 2013
ከማርቆስ ዐብይ
ኢትዮዽያ ሀገሬ ሞኘ ነሸ ተላላ፣
የሞተልሸ ቀርቶ የገደለሸ በላ፣
The Ethiopian government spokesman Shimeles Kemal
እኚ ሰው የኮሚኒኬሸን ጉዳዮች ሚንስትር ዴእታ አቶ ሽመልሰ ከማል ይባላሉ…
አድርባይነት ቀለል ባለ አገላለጽ ማስመስል ወይም ለጥቅም ሲባል ሕሊናን መሸጥ እንደማለት ነው፣፣ ይህ እኩይ ባሕሪ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ቀላል የማይባል እድሜ አስቆጥሯል የሩቁን ትተን የቅርቡን ከጣሊያን ወረራ ቦኋላ ያለውን አሁን እስካለንበት ጊዜ ያለውን ለማየት ብንሞክር እንኳ በጣም ብዙ ነገሮችን መታዘብ እንችላለን።
ጣሊያን ኢትዮጵያን በግፍ በወረረበት ወቅት የክርስቶስን ወንጌል ይሰብኩ ከነበሩ የሐይማኖት አባቶች መካከል በጥቅማ ጥቅም የተደለሉ ጥቂት የሐይማኖት አባቶች በየአውደ ምሕረቱ ለምዕመናን ከመጽሃፍ ቅዱስ ላይ ኤሳው ለምስር ወጥ ሲል ብኩርናውን አሳልፎ ለወንድሙ ለያዕቆብ መሸጡን በመጥፎ ተምሳሌትነት እንዳላስተማሩ ሁሉ ራሳቸው ለቁራሽ እንጀራ ሲሉ ሕሊናቸውን በመሸጥ ከወራሪው ከጣሊያን ጎን በመሰለፍ ለምዕመናኑ በሃሰት በእግዚአብሔር ሃምሳል ኢትዮጵያን ለመታደግ የመጣ ነው በማለት ሕዝቡ ወራሪው ጣሊያንን አሜን ብሎ እንዲቀበል ያግባቡ ነበር።
በዚህ የወረራ ዘመን የንጉሠ ነገሥቱ የቅርብ ባልሙዋል ከነበሩ መኩዋንንቶች እና መሳፍንቶች መካከል ሳይቀር ለጣሊያን ያደሩ ነበሩ፣፣ እነዚህ ሹማምንቶች ህዝቡ ተቃውሞውን በማቆም ይዘውለት የመጡትን እውቀት እና ስልጣኔ በመቅሰም ሀገሩን ያለማ ዘንድ

Friday, December 20, 2013

ባዶ ሳጥን። ከሥርጉተ ሥላሴ


ከሥርጉተ ሥላሴ   21.12.2013
ኢትዮጵያዊነት ለሄሮድስ መለስ በሽታቸው ነበረ። ደፍረን እንናገረው …..
ቀልዴን እንዳይመስላችሁ የእውነቴን ነው። ተረብ እንዳይመስላችሁ ነው የምር። ከልቤ ሙዳይ ያለችውን ሚስጢር ዘክዘክ አድርጌ ላጋራችሁ እንሆ ዛሬ ወደድኩ። የታደለቸው ኩኑ በ15.12.2013 የነገ የሰላም መዲና ሆነች። የአፓርታይድን ግብዕት ለመፈጸም ፍሬ አፍርታ ዘር አንዘርዝራ ጎታዋን በእኩልነት ሞላልታለችና እንደ ጎለጎታ ዎህ ብላ በልበ -ሙሉሉነት ሰከነች። እንሆ … ኩኑ ሰላማዊ ቅዱሳዊ እረፍት ለልጇና ለወዳጇ በክብር ሸለመች። ይጋባታል! ይህ የዓለም ፊኖሚናና አጀንዳ የሆነ የበኽረ አስራታት እናት ናትና ዬምርት ጎታዋ ተትረፈረፈ – በዕውቅና። አደናቆትም በአርቱ ማዕዘናት ተቸራት። ኩኑዬ ልበላት ትቆላመጥ አይደል? ቢያስፈልግም ዬወርቅ ቀለበት አስርቼ ላክ ነው የማደርግላት። የሰላም አባት የእረፍት ቦታ ለትውልዱ፤ የነገም የአፍሪካ ትውፊት። ማለት ቅርስና ውርስ የቅብብል አድባር በመሆን አፈሯ ከበረ – ተባረከ – ተመረቀ። የነፃነት ራህብተኞች ሁሉ ስብከቱን፤ ማህሌቱንና ቅኔውን ከቦታዋ በመሄድ ያጣጥማሉ … ከዛሬ ጀምሮ። ለማግስት ወደ ምስራቃዊዋ የኬፕ ገጠራማ ወደ ኩኑዬ ሚሊዮኖች ይተማሉ ….. ዕምነት – ፅናት – ቅንነት – ይበቃኛል – ቤዛነት – ፍቅር  የሰበለባት ደግ ሰፈር። ማህደረ – ዕሴት! ትልቅ የተግባር ሙዚዬም ይገነባባታል። ዩኒስኮም ይሄኔ አጭቶት ይሆናል። ጽድቅ።
መስታውቷ ኩኑ ተልዕኳውን በተግባር ትማ፤ ለትውልድ አደራን አቅልማ አስማምታ ዳረች። ትንሿ የደቡብ እፍሪካዊቷ መንደር ልክ እንደ ጎለጎታ ፍቅርን በአግልግሏ በአደራ አመሰጥራ ታሪክን በዕንቁ አንቆጥቁጣ አስቀመጠች። የታደለች! መርቋታ! የምን ዝም እዬበሉ እዬጠጡ። ኩኑ – ኩሩ ምህረትን ፈትላ ነገን በተዋበ ጃኖ አለበሰች። ሰላምን ጠርታ ቅንነትን ለድል አቀለመች። መታባበርን ጋብዛ ዓለምን በአንድ ቀለበት በኪዳን አዋውላ ጠመቀች። ፍላጋ አስምራ ለፍትኃት ናፍቆትን ታጠቀች። አማረባት!  አስተሳሰረች …. ኩኑ አስናች – አስቀችም። አንድ ቀን ሄጄ አያታለሁ። እኔም የድርሻዬን ሁለቱን መስኮቶቼ ከፋፍቼ እንዲተነፍሱ አደርጋለሁ። የነፃነት እምነቴንም ቆጣጥሬ ስቀበር አብሮኝ እንዲሆን እናዘዛለሁ …. ታደልኩ።
በመጤ እንደራሴ ሲባክኑ፤ ማንነታቸው አምልጧቸው እንደ ግዑዝ ሞትን ሳያስቡ ያለፉት ሄሮድስ መለስ በመላጣና በተጠ ገጠመኝ ሲወዛወዙ፤  ከተኮፈሱበት ወረድ ብለው በዓለም አደባባይ „ጊዜ ገቢረ ለእግዚአብሄር“ ሆነና በባተሌ ትንታግ፤ የዕንባም ሰማያዊ መልክተኛ፤ መክሊተኛም ግራማቸው ሸሽቶ በቅፅበት ከሰሉ። በጉልበታሙ ዬነፃነት ስንኛዊ ድምፅ ብቻ በርግገው ክብራቸው ለአፍታ ተኖ ተገፈፈ። ጥቂትም ሳይቆዩ ከል ዕንባ የተላኩ የመላእከ ሞት ወታደሮች መንፈሳቸውን በክርኒ ሰልቀው ለህልፈት ዳረጓቸውና ሥጋቸውም ሆነ መንፈሳቸው አፈር ሆነ። እሳቸውን አፋችነን ሞልተን ሞቱ ማለት እንችላለን። አፍር ሆኑ – በሐምሌ 7.2012። በሽታቸው ቀኑ የተሰበረበት፤ አሟሟታቸው ቀኑ የተጣፈበት፤ ቀብራቸው ደግሞ እሬሳ የሌለው ባዶ ሳጥን።  እንዲህ ዓይነት ታሪክ በዬትኛው ሀገር በዬትኛው መሪ ደርሶ ያውቃል?!  ይህ ብቻ በራሱ ቆሞ የሚመሰክረው አንድ የነጠረ ሃቅ አለው። ለኃጥ የወረደ ለፃድቅ ሆኖ ተወዳጁ የጋናው መሪም ወጨፎ ደረሳቸው። ቀን ጠበቃ ነው። ቀን ጥግ ነው። ቀን ለቀን ሰጥቶ ጥቃትን ያወጣል። የበቀል አምላክም እርግማኑን ካለይቅርታ ልኮ ዕንባን ይታደጋል። …. ሊቀ – ሊቃውንቱ አልፃፉትም እንጂ ታምሩስ ታምር ነበር። ለዓለም ህዝበ -ክርስትያን በብራናቸው ከተብው ማወጅ ነበረባቸው። እኛ የትናንትናውን ብቻ እናዘክራለን፤ የትናንት አምላክ ዛሬም

ከወያኔ መንደር ውጡ

December 20, 2013
ዳዊት መላኩ (ከጀርመን)
አቶ አያሌው ጎበዜም እንደምንም  የመምህርነት ስራቸውን ትተው የድል አጥቢያ አርበኛ በመሆን ገብተው ወይ ራሳቸውን ነፃ ሳያወጡ ወይ ህዝቡን በትክክል ሳያገለገሉ እንዲሁ እንደ ውሃ ላይ ኩበት  እመሀል ላይ እንደዋለሉ የማይቀረውን ስንብታቸውን ተሰናበተዋል፡፡ ወያኔ እንደ ሸንኮራ ምጥጥ አድርጎ ተፋቸው፡፡እኔ እስከማውቃቸው አቶ አያሌው ከሌሎች የወያኔ ባለስልጣናት የሚለዮት በሙስና አለመጠርጠራቸው፤ብዙ ማውራት የማይወዱ ሲናገሩም ከባህል እና ከሞራል የማያፈነግጡ፤ለሚኖሩበት ማሀበረሰብ ክብር በመስጠት ሚስታቸው ሳይቀር አብረዋቸው ከሚኖሩት እድርተኞች እኩል መሳተፋቸው ነው፡፡ አቶ አያሌው እንደአባዱላ ገመዳ ብዙ ቤት ገንብተው ለትግሉ ስላስቸገረኝ ውሰዱልኝ ሲሉ አልተደመጡም፡፡እስካሁን ባለኝ መረጃ መሰረት አቶ አያሌው ባህርዳር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 14 አካባቢ በማህበር ተደራጅተው በወሰዱት አንድ ቦታ ቤት እንደገነቡ ነው ፡፡ ዘመድ አዝማዳቸውን ስራ በማስገባት አይታሙም ፡፡የአቶ አያሌው ልጆች እንደ ሌሎች የባለስልጣን ልጆች አሜሪካ እና አውሮፓ ወይም አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ ውድ የግል ትምህርት ቤቶች አይደለም  የሚማሩት፡፡እንደማንኛውም ደሃ ቤተሰብ ባህርዳር ውስጥ ባሉ የመንግስት ትምህርቤቶች ያስተምሩ ነበር፡፡Ayalew Gobeze (Amhara Regional State)
አቶ አያሌው እንግዲህ እነዚህ መልካም ነገር ቢኖራቸውም የተሰጣቸውን መክሊት አባክነው የክልሉ ህዝብ በየቦታው ሲፈናቀል የክልሉ መሬት እንደዳቦ እየተሸነሸነ ሲታደል የተቀመጡባትን ወንበር ላለማጣት በዝምታ ማለፍን መርጠዋል፡፡ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከተጠያቂነት አያድንም፡፡ከሌባ ጋር አብሮ ስርቆት ሂዶ  በቅርብ ርቀት ሲሰርቁ እያዩ ዝም ማለት እና የሰረቀው አብሮኝ ያለው

Wednesday, December 18, 2013

የኢትዮጲያ ሰላም በአንድነታችን ላይ ነው


 
The shadow of a supporter of Ethiopia's Unity for Democracy and Justice party (UDJ) is seen through an Ethiopian flag during a demonstration in the capital Addis Ababa
               የሚያኮራ የሚያስደስት ኢትዮጲያዊ አንድነት ሰሞኑን በተደረጉት የተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ አይተናል:: በሳውዲ አረቢያ እየተሰቃዩ ላሉት እህትና ወንድምቻችን ሀይማኖትና ዘርን ሳንለይ ያሳየነው የአንድነትና የቁጣ መንፈስ በጣም የሚያስደስት ነው:: ይሄ ያሳየነው አንድነት እና ቆራጥነት መቀጠል ሊኖርበት ይገባል:: ካልሆነ ግን የችግራችንን ሥር መንቀል አስችጋሪ ነው:: ሳውዲ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጲያዊያን ሲገደሉ፣ሲደበደቡ እና ሲደፈሩ በኢትዮጲያዊነታችው መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል:: ይሄ አይነቱ ኢሰብሐዊ ጥቃቶች በሰፊው እየደረሰ ያለ ሲሆን አንድነታችንን አጠናክረን ወደ ፊት ካልተጓዝን በተለያየ ቦታና ሀገር ኢትዮጲያዊነት ሊደፈር ይችላል::
       በመጀመሪያ መግለፅ የምፈልገው የኢትዮጲያን ክብር እና ማንነት ያጠፋው ወያኔና አመራሩ ናችው:: ስለዚህ ሁል ጊዜ ለሚፈጠሩት ችግሮች ሆይ ብለን መነሳት ብቻ በቂ መፍቴ አይሆንም ዋናው የችግሩን መንሴ ወያኔን ማስወገድ ነው:: ወያኔ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እህትና ወንድሞቻችን ተሰደዋል፣ተገድለዋል፣ተደፍረዋል ይሄ አዲስ ነገር አይደለም ሁላችንም ቢሆን እየሰማን እያየን የቆየነው ነገር ነው:: በአሁኑ ሰሀት በሳውዲ አረቢያ እየተደረገ ያለው ግፍ በዛ እንጂ በፊትም የነበረ ነው::የወያኔ አገዛዝ በሀገር ፍቅር ወይም በአንድነት ላይ የተመሰረተ አይደለም:: ይሄን በደንብ አድርጎ ለብዙ  አመታት አሳይቶናል:: የእናትና የአባቶቻችንን መሬት ለበአድ ሀገር ተወላጆች በመሸጥ፣መሀበረሰቡን በዘር እና በሀይማኖት በመከፋፈል፣እህትና ወንድሞቻችንን ለበአድ ሀገር አሳልፎ በመስጠት እና በመሳሰሉት ማየት ይቻላል::
 የአንድነታችን  መላላት መንሴወች እና መፍቴያችው ያልኩዋችውን ላብራራ
         አንደኛው እንደ ሰው እናም እንደ ኢትዮጲያዊ ለሚደርሱብን ኢሰብሀዊ ድርጊቶች አይሆንም፣አይደረግም የሚል ቆራጥ መንፈስ በውስጣችን መመንመኑ :: ይሄ ወደ ምን ያመራል ብንል ለገንዘብ እና ላአንዳንድ ጥቅማ  ጥቅሞች አገርን አሳልፎ ወደ መሸጥ:: ሰው እንደመሆናችን መጠን ቆም ብለን ልናስብ ይገባል  የወያኔ መንግስት የህዝብ  ጥርቅም መሆኑን:: ህዝብ ደግሞ የእያንዳንዱ ሰው ስብስብ ነው :: ስለዚህ እንደ ሰው ወያኔ ለሚያደርስብን ጥቃቶች አይሆንም ካልን ወያኔ የሚቀጥልበት ምንም ምክንያት አይኖርም:: ህዝብ የመረጠው መንግስት ደግሞ ለህዝቡ አንድነት የቆመ ነው::
   ሁለተኛው የወያኔ የአገዛዝ ስልት ነው:: በህዝብ ያልተመረጠ መንግስት(ወያኔ) ስልጣን ላይ ለመቆየት የተለያዩ  ጫናዊ የአገዛዝ ስልቶችን ይጠቀማል:: ከሁሉም የሚከፋው ዘርን ከዘር  እና ሀይምኖትን ከሀይማኖት  በማጣላት የህዝቡን አንድነት የሚበታትኑት ነው:: ለዚህም ምስክሩ ኢትዮጲያን ለቀው የሚሰደዱ ሰዎች የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ችግር ያላችው ብቻ አይደሉም ጥሩ

“438 Days” in Ethiopian custody – a book by Swedish Journalists

Wednesday, 18 December 2013
Journalists Schibbye and Persson
By: Yusuf M Hasan (somalilandsun)
Somalilandsun – The Authors of “438 DAGAR” Martin Schibbye, and Johan Persson, which is a book detailing their “438 Days” in Ethiopian custody and related experiences have now turned to exposing the ills they perceive to be ongoing in the Ogaden Region.
In an exclusive interview with journalist Mohamed Farah of Ogadentoday Press the two Swedish scribes say their motivation to pursue information on the region some refer to as “Ethiopia’s Darfur” or “Africa’s Palestine” by the burning desire to bring to light inhuman activities that were known but craftily what hidden from the International Community.
Describing their arrest by Ethiopian Counterinsurgency forces operating in the Ogaden region against the Ogaden National Liberation Front-ONLF that led to the 438 Days” in Custody Journalist

Tuesday, December 17, 2013

Menilik II & Mandela vs. Mengistu & Meles – By Robele Ababya


 

 

By Robele Ababya, 17/12/2013
I would like to start writing this piece with this quote attributed to Sir Isaac Newton in his own right as one of the giants in mathematics and classical physics: “If I have seen further it is by standing on the shoulders of Giants.”
MinilikIntroduction
This article is not meant to compare historical events that took place a century apart. The piece is merely a tribute to colossus fighters for freedom from oppression in their own times. This approach provided the opportunity to illustrate what attributes Menilik II and Mandela  had in common, such as their reliance on outstanding feats of their heroic ancestors.
The duo are now at their final resting home in heaven leaving behind a laudable legacy that would take the present and future generations forward through the complex world where, as Sir Isaac Newton said: “What we know is a drop, what we don’t know is an ocean.”

Menilik II
 
In the 19th century (1896) Emmye Menilik II won the victory of the Battle of Adwa that put Ethiopia on the world map as an independent country. The victory shocked European powers, which had no choice but recognize Ethiopia as a free and independent country and establish or bolster their diplomatic missions in Addis Ababa. This was an epic achievement by Menilik II that subsequently

“ሕወሓት ከመለስ ሞት በኋላ እየተዳከመ ያለ ድርጅት ነው፤ ኢህአዴግ ለዘለዓለም መግዛት አለብኝ የሚል ድርጅት ነው” ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ


ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ከህወሓት ጋር 17 ዓመታት በትግል ያሣለፉ እና ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዷ ነበሩ፡፡ በ1993 ዓ.ም ከፓርቲው ከተሰናበቱ አባላት አንደ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የ“አረና” ፓርቲ አባል የሆኑት ወ/ሮ አረጋሽ በአጠቃላይ ጉዳዮች ዙሪያ ከ“ሎሚ” አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ጋር ያደረጉት ቆይታ የመጀመሪያ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
ሎሚ፡- የኢህአዴግ ጭቆናና፣ አፈና፣ የተንሰራፈው በመላው ሀገሪቱ ነው የሚል አቋም ካላችሁ፣ ብሔር ተኮር ፓርቲ የመሰረታችሁበት ምክንያት ምንድነው;
አረጋሽ፡- ፓርቲ የሚመሰረተው በአካባቢ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ መሰረት አድርጐ ነው፡፡ ተጨባጭ ሁኔታ ስል የማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ሰብዓዊ መብት፣ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመጥቀስ ፈልጌ ነው፡፡ ማንኛውም ድርጅት በዚህ መልኩ ነው የሚመሰረተው፡፡ አረናም በዚሁ መሠረት የተመሠረተ ፓርቲ ነው፡፡
aregash adane 2
ከሕወሐት ክፍፍል በኋላ አረና ሲደራጅ፣ ለአገራችን የታገልንለት ዓላማ ሙሉ በሙሉ ስላልተሣካ፣ ያልተሣካው እንዲስተካከል አለያም የተሻለ ለማድረግ የራሣችንን ጫና ማሣደር አለብን ብለን ነው አቋም የያዝነው፡፡ ስንደራጅ ሀገራዊ ፓርቲ የመመስረት ዓላማም ፍላጐትም ነበረን፡፡ ነገር ግን በነበርንበት ሁኔታ አገራዊ ድርጅት መመስረት ቀላል አልነበረም፡፡ ጠንካራ ርዕዮተ ዓለም፣ በጣም ወሣኝ አባላት ያሉት አገራዊ ድርጅት መመስረት አሁንም ቢሆን አስቸጋሪ ነው፡፡ ሀገራዊ ድርጅት የመመስረት ፍላጐት ቢኖረንም የነበርንበት ተጨባጭ ሁኔታ አልፈቀደልንም፡፡ በተግባር ስንመለከተው የብሔረሰቦች መብት ሙሉ ለሙሉ ባይከበሩም፣ ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት ሁኔታዎች እስኪፈቅዱልን ድረስ ብለን አረናን መሰረትን፡፡
ይህን ካደረግን በኋላ አረናን ይዘን ቁጭ አላልንም፡፡ ሀገራዊ ፓርቲ ካልተመሠረተ የትግራይም ይሁን የሌላው ብሔር ብሔረሰቦች ችግር ይፈታል ብለን አናምንም፡፡ ሀገራዊ ፓርቲ የሚመሠረትበትን ሁኔታ መፍጠር አለብን ብለን ከሌሎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ህጋዊ እውቅና ካላቸውና በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉ ፓርቲዎች ጋር በአጭር ጊዜ ውይይት ጀመርን፡፡ መድረክ በሚባለው ድርጅትም

Monday, December 16, 2013

በሕወሓት አፈና ቢፈተንም ዓረና መድረክ በማይጨው ሕዝባዊ ስብሰባ አደረገ


 
አብርሃ ደስታ ከመቀሌ
ባለፈው ቅዳሜ ዓረና መድረክ በጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ለመሳተፍ ወደ ማይጨው ከተማ ተጉዤ ነበር። ከመቀሌ -ማይጨው በመኪና የሦስት ሰዓት ጉዞ ነው። ከሰባት ዓመት በፊት የማውቃት ማይጨው ምንም አልተቀየረችም። ብዙ የህወሓት ባለስልጣናት እዛው ማይጨው ነበሩ። ስብሰባዎችና ስልጠናዎች ነበሯቸው።
Arena-Tigray-logoቅዳሜ ከማይጨው ወጣቶች ጋር ተገናኝቼ ነበር። ወጣቶቹ ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ይፈራሉ። የሰለማዊ ትግል ዉጤታማነት ይጠራጠራሉ። ህወሓት በምርጫ ስልጣን ሊያስረክብ ይችላል ብለው አያምኑም። በሰለማዊ መንገድ ከሚቃወሙ በትጥቅ ትግል ቢሳተፉ ይመርጣሉ። ምክንያቱም በትጥቅ ትግል ህወሓት ከስልጣን የሚባረርበት ዕድል ሊኖር ይችላል ብለው ያስባሉ።
በማይጨው የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችም (በተለይ መምህራንና የግብርና ሰራተኞች) በስርዓቱ ቅሬታ አላቸው። የራያ አከባቢ ተወላጆች የሆኑ የህወሓት ካድሬዎችም በስርዓቱ ደስተኞች አይደሉም። ሁሉም ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ዓረና ህወሓትን ታግሎ ሊያሽንፈው ይችላል የሚል እምነት የላቸውም። በራያ ቦታ የሚገኙ የህወሓት አባላት (የራያ ተወላጆች) ህወሓትን ማሸነፍ የሚችል ተቃዋሚ ፓርቲ ካገኙ ህወሓትን እንደሚቃወሙ ይገልፃሉ።
የህወሓት መሪዎችም ይህንን ያውቃሉ። እንደዉጤቱም ህወሓት ከሌላ አከባቢ ታማኝ ካድሬዎች እየላከ የራሱ አባላት ይሰልላል፣ ይቀጣል፣ ያባርራል። በዚህ መንገድ የራያ ህዝብ በራሱ ሰዎች እንዲበደል ይደረጋል። የራያ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ለእንጀራቸው ሲሉ ህዝብ ይበድላሉ። ህዝብ ካልበደሉ ይቀጣሉ፣ ይባረራሉ፣ ሌላ

“ወደ ፖለቲካው ተመልሻለሁ” – አቶ ልደቱ አያሌው


በምርጫ 97 በፊት ኢትዮጵያዊው ማንዴላ ተብለው እንዳልተሞካሹ ሁሉ ከምርጫ 97 በኋላ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አይንህ ለአፈር ከተባሉት ፖለቲከኞች መካከል አንዱ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የቀድሞው የኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው ወደ ፖለቲካው መመለሳቸውን አስታወቁ። “ለትምህርት ከ2 ዓመታት በላይ በውጭ ሃገር በመቆየቴ እንዲሁም ከኢዴፓ ሃያ አምስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ብሆንም፣ በጠቅላላ ጉባኤ ከሊቀመንበርነት ስለወረድኩ የፓርቲው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ስለማልመራ” ከሚድያው ጠፍቻለሁ ያሉት አቶ ልደቱ ወደ ፖለቲካው መመለሳቸውን ያስታወቁት በአዲስ አበባ ከሚታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
lidetu
“በኢትዮጵያ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገቱን መካድ ስህተት ነው፤ እድገቱ ዘላቂነት እንደሌለው አለመገንዘብም ስህተት ነው” የሚሉት አቶ ልደቱ “ሦስተኛ አማራጭ” የተሰኘ የኢዴፓ አቋምን በቃለ ምልላቸው ላይ ገልጸዋል።
በቃለምልልሳቸው ላይ ኢሕአዴግ አመጣሁት ስለሚለው ዕድገት አቶ ልደቱ “”የእድገቱ መጠን መንግስት እንደሚለው ሳይሆን፣ ስምንትና ሰባት ፐርሰንት ይሆኖል ብዬ አምናለሁ፡፡ ይሄም ቢሆን መጥፎ እድገት አይደለም፤ ጥሩ እድገት ነው፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ ደረጃ ላለ ድሃ አገር ከስድስት ፐርሰንት በታች የወረደ እድገት፤ ኢኮኖሚው እንደተኛ (ሪሴሽን ውስጥ እንደገባ ነው የሚቆጠረው፡፡ በጣም በከፍተኛ ደረጃ ማደግ ነው የሚጠበቅብን፡፡ የሌሎችም አገራትም ታሪክ ያንን ነው የሚያሳየው፡፡ እንደ አሜሪካና እንደ እንግሊዝ አገር አይነት ትልቅ ኢኮኖሚ ውስጥ ሶስትም አራትም ፐርሰንት ማደግ ከባድ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ኢኮኖሚ ተይዞ ግን፤ ደብል ዲጂት ማደግ ይቻላል፡፡ መጣ የሚባለው እድገት በህብረተሰቡ ህይወት ውስጥ መታየት አልነበረበትም ወይ? ሊታይም ላይታይም ይችላል፡፡ አንድ ኢኮኖሚ ማደግ ሲጀምር ሁሉንም ህብረተሰብ ይጠቅማል ማለት አይቻልም፡፡ ይሄ በየትም አገር ሆኖ አያውቅም፡፡ እንኳን ዘጠና ሚሊዬን ህዝብ ያለበት አገር ይቅርና፣ 3ሚሊዮን ህዝብ ባለበት አገርም ኢኮኖሚው ማደግ ሲጀምር ሁሉም ህብረተሰብ ተጠቃሚ ይሆናል ማለት አይደለም፡፡ ቀስ በቀስ ነው ተጠቃሚው እየበረከተና እያደገ የሚመጣው፡፡ ስለዚህ አሁን

Mandela’s Message to Ethiopia’s Youth: Never give up…!

December 16, 2013
by Alemayehu G. Mariam*
Africa’s Wise Lion and Ethiopia’s Restless Cheetahs—Never give up and keep on trying to build your Beloved Ethiopian Community!
Mandela’s Message to Ethiopia’s Youth
December 15, 2013. It is the saddest day of the year for me. Nelson Rolihlahla Mandela was finally interred with state honors in Qunu, a small rural village in South Africa’s Eastern Cape Province. He spent the “happiest days” of his life there as a shepherd. He returned to Qunu after a long life, a long imprisonment and a long walk to freedom to join his  ancestors. The young shepherd of Qunu returned to his final resting place as the revered, loved and respected shepherd of his people. I bid him farewell. May he rest in eternal peace!
December 15, 2013. It is the happiest day of the year for me. I am just outside Washington, D.C. at a town hall meeting to welcome Semayawi (Blue) Party and its young Chairman Yilikal Getnet. I am here to celebrate Ethiopia’s dynamic and striving young people; to honor them and demonstrate my unflagging and unwavering support for their nonviolent struggle against oppression and human rights

Sunday, December 15, 2013

Mandela laid to rest in Qunu, ending journey that transformed South Africa

December 15, 2013
(CNN) — Nelson Mandela was laid to rest in his childhood village of Qunu on Sunday, marking the end of an exceptional journey for the prisoner turned president who transformed South Africa.
Mandela was laid to rest in the afternoon, when the sun is at its highest.
Under the scorching sun, a military escort accompanied his coffin to the burial site and took off the national flag that draped his casket. White wreaths sat around it.
His widow, Graca Machel, and others watched from under a tent as helicopters carrying flags whizzed past.
“Now you have achieved the ultimate freedom in the bosom of God, your maker,” the officiator said.
Tribal leaders clad in animal skins joined dignitaries in dark suits at the burial grounds atop a hill overlooking Qunu valleys.
Before making their way to the site, mourners attended a service in a tent set up for the event. Ninety-five candles glowed behind his casket, one for each year of his life.
Mandela died December 5 after a recurring lung infection and declining health.
The service
The service started with a somber military procession wheeling his casket into the tent. Residents

Tamrat Layne: Another Botched Marxist Rollout

December 14, 2013
by Mark Baisley
Meles Zenawi and Tamrat Layne were born just months apart in 1955
The political philosophy of German sociologist Karl Marx inspired the imaginations of many aspiring revolutionaries. While he did not live to see his theories played out on the large scale of the Soviet Union, Marx did leave volumes of written instructions for his followers in The Communist Manifesto and Das Kapital.
During the mid-1950s, while Fidel Castro and Che Guevara were busy installing the first communist oligarchy in the Western Hemisphere, a parallel partnership was emerging half-way across the globe in eastern Africa. Meles Zenawi and Tamrat Layne (pronounced “lie-nay”) were born just months apart in 1955 in the northern market villages of Ethiopia.
As the boys matured into adulthood, their close friendship was solidified in a shared admiration of Karl Marx. They read and reread every Marxist writing that they could get their hands on. By the

Saturday, December 14, 2013

Remembering December 13th: The Anuaks Massacre

December 14, 2013

Let us take this day of sorrow and make it a day of healing among all peace-loving Ethiopians

Anuak Justice Council
December 13, 2013 marks the ten-year anniversary of the brutal massacre of 424 disarmed Anuak in Gambella, Ethiopia by Ethiopian National Defense Forces armed with guns and militia groups armed with machetes. Not just the families of the victims, but all Anuak, will forever remember that dark day that brought so many pains, tears and suffering.December 13, 2013 marks the ten-year anniversary of the brutal massacre of 424 disarmed Anuak in Gambella, Ethiopia
Even after ten years, some widows, some fathers, some mothers and children are still waiting to bury their loved ones properly. Some day their bodies, which were buried in mass graves, will be exhumed and buried with proper respect by their families and loved ones. Some day a memorial of remembrance may be erected in Gambella in their honor, to remind people that behind every name on that memorial, is a human life, given as a precious gift from God, our Creator.
Such memorials may be erected all over Ethiopia where innocent lives of Ethiopians have been taken. Some day, a large monument—a wall of shame—could be erected in Addis Ababa with the

Ethiopian officer recalls training Mandela


BY ELISSA JOBSON, DECEMBER 13 2013,
Gen Fekade Wakene. Picture: ELISSA JOBSON
Gen Fekade Wakene. Picture: ELISSA JOBSON
ADDIS ABABA — “He was extremely tough, extremely vigilant, intelligent and loveable. So loveable,” says Col Fekade Wakene of the late Nelson Mandela — the student he schooled in guerrilla combat in July 1962.
“The training was so rigorous and he never complained, every time smiling. Other soldiers I trained would get so angry, but Mandela was always charming.”
Col Fekade, now aged 77, sits quietly and solemnly in the front room of his modest home in Addis Ababa’s Little Mogadishu area. He straightens his scarf which is striped red, gold, white, blue, green and black — the colours of the South African flag. It was a gift from South Africa’s minister of arts and culture, he says. “Every time I think about South Africa, about Mandela, I always want to wear this scarf,” Col Fekade explains.
Nelson Mandela's Ethiopian passport
Nelson Mandela’s Ethiopian passport
In 1962, he was a sub-lieutenant in the Fetno Derash, a special battalion of the Imperial Ethiopian

ኃያሉ አፄ ሚኒሊክ ለሴቶች እኩልነት ተግባራዊነት ዓለምን የቀደሙ ንጉሥ


ከሥርጉተ ሥላሴ 
ስርጉተሥላሴ
ስርጉተሥላሴ
ያን ዘመን ሳስበው ዛሬን መስለችን ያስለቅሰኛል። ያን ፈርጣማ ዘመን ሳስታውሰው ዛሬ ውስጣችነን መሳሳቱ ያቃጥለኛል። ያን ገድላማ ብቁ፣ ሥልጡን፣ ልዑቅ የአመራር ጥብብ ሳናግረው ግን መጽናናትን፣ ሙላትን ያጎናጽፍልኛል። ክብራቻን፤ ማንነታችን፤ ተፈሪነታችን፤ መሪነታችን፤ ብልህነታችን፤ እርግጠኛ ያደረጋል፤ የቀደምቶቹ ብቃት የሰማይ ገደል ለዛሬ ፍንጣቂ ማስተዋል ቢልክልን አምላኬ ምን አለበትም እላለሁ። የባዕዳን ግራሞት ጭብጥ፤ የእርስ በርስ ችግራችውን ዋጥ አድርገው በጋራ ቆመው ትንግርትን ሰማዕታት ማዘከራቸው የህሊናችን ዳኛ ሆኖ እኛን ሊገራን ባለመቻሉ ግን የልቤ ክናድ ይላል። ነገ ሌላ ቀን ነውና ነገን እንዲመርቅልን ህይወቱ ያላቸው አበው ሱባዬ ቢይዙበት ምኞቴና ናፍቆቴ ነው … አንደ ዕምነታቸው።
ዓለም ስለ ሴቶች ብቃት ብጣቂ እውቀት ባልነበረበት ጊዜ የኛው አፄ ኃያሉ ንጉሥ ሚኒሊክ ደማቸው – መንፈሳቸው – ሙሉዕ ፈቃድ ሰጥቶ ተግባር ላይ የዋለ በኽረ ጉዳይ ነበር የሴቶች እኩልነት። ኢትዮጵያ ሚስጢር ናት። ኢትዮጵያ ገድል ናት። ኢትዮጵያ ዓለም – ዓቀፍ ህግ ናት።  ኢትዮጵያ የቀደመች ሥልጡን መምህርት ናት። በዘመኑ የጣሊያን ተጋነት፤  የኢትዮጵያ ጥበበኛው መሪ የአፄ ሚኒሊክ አመራር ደግሞ ዕርቅና ሰላም ፈላጊነት ዓለምን ያሰደመመ መረቅ ትውፊት ነበር። ምርኮኛን ተንከባክቦና መርቶ ወደ

Friday, December 13, 2013

የራስን እድል በራስ መወሰን፣ እርስ በርስ እስከማጣላት… ሌላው ኢትዮጵያዊ የተዋረደበት፤ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን – በኦጋዴን!


የራስን እድል በራስ መወሰን፣ እርስ በርስ እስከማጣላት…
ሌላው ኢትዮጵያዊ የተዋረደበት፤ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን – በኦጋዴን!
ዘንድሮ በኢትዮጵያ ተከበረ የተባለውን የብሄሮች  ቀን ምን ያህሎቻችሁ እንደተከታተላቹህ አላቅም። ላላያችሁት ግንዛቤ ለመፍጠር ያህል… ዘንድሮ በአሉ የተከበረው ሱማሌ ክልል፣ በኦጋዴን ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን በመንገር ወጋችንን እንጀምራለን። ይህ ዝግጅት እስከዛሬ በትግራይም፣ በአማራውም ክልል ተደርጓል… ሆኖም በአሉ ላይ ሁሉም የየብሄሩን ባህል ለማሳየት ሲጥር እንጂ፤ አንደኛው ብሄር ሌላውን ሲሰድብ ያየንበት አጋጣሚ አልነበረም። የዚህ አመቱ የብሄር ብሄረሰቦች ወይም የብሄረተኞች ቀን ሌላውን ኢትዮጵያዊ በመውቀስ ላይ የተመሰረተ ነበር።
“አማራው፣ ደገኛው፣ የመሃል አገር ሰው…” እያሉ ቀጠሉ አስተያየት ሰጪዎቹ። በአሉን ምክንያት በማድረግ በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት ታዳሚዎች ወቀሳቸውን ቀጠሉ፤ “የመሃል አገር ሰዎች ‘ሽርጣም ሱማሌ’ እያሉ ይጠሩን ነበር” አለ። እኛንም በሃሳብ ወደኋላ መለሰን። የመሃል አገር ሰው ይህንን ቃል አይጠቀምበትም ለማለት አይደለም። ነገር ግን “ሽርጣም ሱማሌ” የሚለውን ቃል መስማት የጀመርነው፤ በኢትዮጵያ እና ሱማሌ ጦርነት ወቅት ነው። “ሽርጣም ሱማሌ” የሚለውን አባባል ሁሉም የመሃል አገር ሰው እንደማይጠቀምበት ሁሉ፤ በቴሌቭዥን መስኮት ላይ ብቅ ብለው ሌላውን ኢትዮጵያ የሰደቡት እና ያሰደቡትም መላውን የኢትዮጵያ ሱማሌ እንደማይወክሉ እናውቃልን። በመሆኑም ይህ ጽሁፍ በሁሉም የኢትዮጵያ ሱማሌዎች ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን፤ የማያውቁትን ታሪክ ለማሳወቅ ያህል የተዘጋጀ መሆኑን ልብ ይበሉ።
 (በዳዊት ከበደ ወየሳ –  ጋዜጠኛ)
ethiopia somalia
በ1969 ዓ.ም. ሱማሌ ኢትዮጵያን ስትወር፤ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አፈናቅለዋል፤ ገድለዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩትን ማርከው ወስደው አገራቸው ውስጥ አስረዋል። ሱማሌዎች ይህንን በሚያደርጉበት ወቅት ታዲያ ሽርጥ እንጂ ሱሪ ታጥቀው አይደለም። በዚያን ወቅት ታዲያ የኢትዮጵያ ልጆች ዳር ከዳር “ሆ” ብለው ሲነሱ፤ በወገናቸው ላይ የደረሰው በደል ቢያንገበግባቸው፤ “ይሄ

ጄነራል ሳሞራ የኑስ በውጭ ተቃዋሚዎች የመለስን የበላይነት መስክረዋል አሉ


(ዘ-ሐበሻ) ኢሕአዴግ ለይስሙላ ያከብረዋል እየተባለ በሚተቸውና ለ8ኛ ጊዜ የተከበረውን የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የሕገ መንግሥት ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ መንግስት ባሳተመው ‘ሕብረ ብሔር’ መጽሔት ላይ ቃለ ምልልስ የሰጡት የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ የኑስ መለስ ከሞተ በኋላ በውጭ ያሉ ተቃዋሚዎች የሟቹን አቶ መለስ ዜናዊን የበላይነት መስክረዋልና እናመሰግናቸዋለን አሉ። በሰራዊቱ ውስጥ እኩልነት እንዳለ መናገራቸውም ብዙዎችን አስገርሟል።
Samora Yenus
በከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ ነው በሚል በተደጋጋሚ ተጽፎላቸው የነበሩትና አሁንም ህክምና ሁልጊዜ እንደሚከታተሉ የሚነገርላቸው ጄነራል ሳሞራ ከመንግስታዊው መጽሔት “የቀድሞው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈተ ሕይወታቸው በድንገት ከተሰማ በኋላ በውጭ የሚገኙ አንዳንድ ፀረሰላም ኃይሎች እና አንዳንድ ተቃዋሚዎች ኢትዮጵያ ለሽብርና ለሌሎች ፀረ-ሰላም ተግባር መጋለጧ አይቀርም ሠራዊቷም መዳከሙ አይቀርም በማለት ሲገልጹ ነበር። ይህ ሊሆን ያልቻለው ለምንድ ንነው ይላሉ? እነዚህ ወገኖች ይህን ተመኝተዋል ነገር ግን ያልሞከሩት ከምን አንፃር ነው?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “ከመለስ በኋላ ሠራዊቱ ይዳከማል ብለው ማሰባቸው የመለስ አስተዋፅኦ ጠንካራ ሠራዊት እንዲኖር፣ ጠንካራ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ኃይል እንዲኖር ያስቻለ ስለመሆኑ እውቅና መስጠት ስለሆነ እናመሰግናለን።” ካሉ በኋላ ቀጥለውም “ምክንያቱም መለስ ይህቺ አገር ጠንካራ የመከላከያ ኃይል እንዲኖራት ወሳኝ ድርሻ ነበረው ብለው ስላመኑ ነው ይህንን ማንሳት የጀመሩት፡፡ ይህን ማሰብ በመጀመራቸው ደግሞ መመስገን ይኖርባቸዋል፡፡” ብለዋል።
ሳሞራ በመንግስታዊው ጋዜጠኛ ለቀረበላቸው ለዚሁ ተመሳሳይ ጥያቄ በሌላ በኩል የአንድ ሰራዊት ጥንካሬ የሚለካው በሰራው አንድ ሥራ ብቻ አይደለም። ሠራዊቱ ይህቺ አገር እስካለች ድረስ አብሮ ይኖራል። ምክንያቱም ተቋሙ ቀጣይ ነው። ተቋሙ ለሁለት ነገር ብቁ መሆን አለበት። አንደኛ ለወቅታዊ ግዳጁ፣ ሁለተኛ ደግሞ ለወደፊት ለሚሰጥ ግዳጅ ብቁና ዝግጁ መሆን አለበት። የእያንዳንዱ አመራር ተልዕኮም ይሄ ነው። በተለይ የከፍተኛ አመራሩ ተልዕኮ ይህንን ማረጋገጥ ነው። ይሄን እንዴት እንፈፅመዋለን ለሚለው ደግሞ ሶስት መሰረታዊ ሥራዎችን በመሥራት ነው።
ዋናውና ወሳኙ የሰው ኃይሉን ማዕከል ያደረገ ሥራ መሥራት ነው። የሰው ኃይሉን ማብቃት። ቴክኒካዊና ሙያዊ እንዲሁም አካዳሚያዊ ብቃቱን ማሳደግ፣ ሳይንሳዊ ዕውቀቱን ማዳበር፡፡ እንግዲህ ሶስት የአቅም ግንባታ ሥራ መሥራት ዋነኛው ሆኖ የሰው ኃይል ማዕከል ያደረገ የአቅም ግንባታ ሥራ መስራት ያስፈልጋል። ሁለተኛው ሥራ በአደረጃጀቱና አሰራሩ ሕዝባዊ ባህሪውን እንደጠበቀ ከተልዕኮውና ከባህሪው የሚስማማ አደረጃጀትና አሰራር ያለው እንዲሆን ማድረግ ነው። አደረጃጀት አቅም ፈጣሪ ነው። አደረጃጀት ለዘለዓለም የሚኖር አይደለም። ከሁኔታው ጋር እየዳበረ አቅም እየፈጠረ የሚሄድ መሆን አለበት። አሰራሩም በተመሳሳይ ከሕዝባዊ ባህሪውና ከተልዕኮው የተጣጣመ አሰራር ዴሞክራሲ ያዊና ደስተኛ ሕይወቱን በአስተማማኝ የሚጠብቅ፣ የግዳጅ አስተሳሰቡንና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰቦችን የሚያዳብሩ አሰራሮችን ማረጋገጥ ማለት ነው። አደረጃጀቱም፣ አሰራሩም፣ የሰው ኃይሉም ሦስቱን ሥራዎች በመሥራት ነው ለተጨባጭ ግዳጅም ሆነ ለወደፊት ለሚሰጠው

Thursday, December 12, 2013

ጠርዝ ላይ ያለ ስጋቴ – በመንትዮሽ። ከሥርጉተ ሥላሴ


ከሥርጉተ ሥላሴ
12.12.2013
ስጋት እንደሚፈቀድልኝ አስልቼ ሃሳቤን ንፉግ ሳልሆን ልገልጽ ወሰንኩ። መወሰንና መቁረጥ መልካም ናቸው። ካሰቡት
የሚያድርሱ ሰጋሮችና ገሮችም።
andu-family-45
በሌላ በኩልም ከመንፈስ መታከት ይታደጋሉ – ይመስለኛል። እመቤት ነፃነትና ፊታውራሪ ሂደት እውኃ በሚያደርግ ፋስ ለማን አዘነሉት?! የፊታውራሪ ሂደት የትርታ – ትብብር አማ ስንቱን ገበርዲን ስንቱን ሙሉወርድ ዋጠው? ስንት አቅም ባከነ – ስንት ፍቅርስ አለቀሰ? ስንት አብሮነትስ ተከፋ? ሰረዘው … ሰወረው? ፊታውራሪ ሂደት ብዙም ሳንርቀው ግራው – ቀኙ – ማዕከላዊነትን አግቶ ወይንም ነካክቶ። የቅርቡን ስናስበው ሁለት ምርጫ ይዞ ቀረቦ ነበር። ዘንባባ ወይንስ ሳንጃ በማለት አሳፈን። እኔ ከአጠው ቋጥኝ አፋፍ ላይ ሆኜ ናዳውን ለእህትና ወንድሜ፤ እህትና ወንድሜም አጸፋውን በመልቀቅ ተጠን። የባሰው ግን ሺዎች አለፉ፤ በእስር ማቀቁ … ስንት የፍቅር ቤት – ትዳር ተፈታ፤ ተናደ ~~~ አብሶ ህፃናት የወላጅ ናፍቆት አሰቃያቸው፤ ፍቅርና እንክብካቤ

«ድምጽ አልባው አሳዛኝ የወገኖቻችን ለቅሶ በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ!»


በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መዝናኛ ክበብ ሰራተኞች ሰንደቃላማችን በተሰቀለበት ግቢ ግፍ እና በደል እየተፈጸመባቸው መሆኑን ገለጹ 
በኢትዮጵያን ሃገሬ ከጅዳ ዋዲ
በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ ሁለት የጸጥታ ጥበቃዎችን ጨምሮ ከ13 በላይ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በስሩ እንደሚገኙ የሚነገርለት ይህ የመዝናኛ ማዕከል ከተቆርቆረ ሁለት አስርተ አመታትን ቢያስቆጥርም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በተለያዩ ሰንካላ ምክንያቶች ከትርፋማነት ይልቅ ኪሳራ፤ ከእድገት ይልቅ ውደቀትን እያቀነቀነ አሁን ላለበት ደረጃ መድረሱን የሚናገሩ እማኞች በሰራተኞቹ ላይ እየተፈጸመ ያለው በደል ከመቸውም ግዜ በላይ እየከፋ መምጣቱን ገልጸዋል።
saudi 1
ይህ የኮሚኒቲ ማህበር ካፍቴሪያ ማዕከል ዛሬ ላለበት አሳፋሪ ደረጃ ምክንያት መሆኑ የሚነገረው በተለያዩ ወቅቶች በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ጀርባ ታዝለው ያለችሎታቸው አመራር የሚሆኑ ግለሰቦች ከኮሚኒቲው ካፍቴሪያ ሰራተኞች ጋር በቅርበት

THE FUTURE IS IN OUR HANDS


December 2013
Imru Zelleke.
Lij Imru Zelleke, Picture: http://imruzelleke.com/
Lij Imru Zelleke,
Picture: http://imruzelleke.com/
The high fever that has spread the all over the Diaspora seems to have simmered down to a tolerable level. Most of refugees in Saudi Arabia have been repatriated home and the few left will get back soon. Those still in jeopardy are the ones under care of the UNHCR in Yemen, for whom a permanent residence is to be found. Otherwise Ethiopians refugees are in dire and precarious conditions in Middle East and African countries  where they are abused and often killed.
The refugees that have returned seem to have fallen from the frying pan into the hot brazier.  It is said that upon arrival home whatever processions (money, jewelry, valuable items) they have manage to save are confiscated by the regime, and they are forced to go back to their Kilil of origin; places

Wednesday, December 11, 2013

የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ፪ – ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)


 
harar
ባለፈው ሳምንት የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካን ተጨባጭ እውነታዎችን ቃኝቼ ተከታዩን ክፍል በይደር አቆይቼው እንደነበረ ይታወሳል፤ እነሆም ዛሬ እንዲህ እቀጥላለሁ፡-
ሐረር እንደ ማሳያ
(መቼም ኢህአዴግ በብቸኝነት የሚኩራራበት የፖለቲካ ‹ስኬት›፣ ለዘመናት አንድ ሆኖ የኖረ ሕዝብን ‹ብሔር ብሔረሰቦች› በሚል ከፋፋይ የ‹ክርስትና ስም› እጥምቆ በአደባባይ ማስጨፈር ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ርግጥ ነው በአንድ ወቅት በፍትህ ጋዜጣ ላይ ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከ መጨፈር›› በሚል ርዕስ የታተመ መጣጥፍን ተከትሎ ‹ፀረ-ብሔር ብሔረሰቦች› ተደርጌ በተመሰረተብኝ ክስ ፍርድ ቤት መመላለሴ ዛሬም ድረስ መቋጫ አላገኘም፤ ርግጥ ነው ኢትዮጵያውያን ወንድም እህቶቼ በስታዲዮሞች እየተሰባሰቡ የራስ ፀጉራቸው ላይ ላባ ሰክተው፣ ቆዳ አገልድመው እየዘለሉ ትርኢት ከማሳየት ባለፈ የመልካም

Racism in Israel: Uproar as Ethiopian MK denied chance to give blood


Magen David Adom applies regulation banning donations from those who lived in countries with high rate of AIDS
A Knesset member born in Ethiopia was not allowed to donate blood at Israel’s parliament building Wednesday, setting off a firestorm of criticism over the denial by the Magen David Adom rescue organization.
MK Pnina Tamano-Shata in the Israeli parliament on November 19, 2013. (photo credit: Flash90)
MK Pnina Tamano-Shata in the Israeli parliament on November 19, 2013. (photo credit: Flash90)

Knesset Speaker Yuli Edelstein ordered MDA banned from setting up blood donation campaigns at the Knesset building after Yesh Atid MK Pnina Tamanu Shata, and Prime Minister Benjamin Netanyahu called for an investigation into the incident.
The furor began when Shata, who moved to Israel at age 3, arrived at an MDA blood drive being held

No More Green Terror in Saudi Arabia!!


 by Tedla Asfaw
Tuesday Dec. 10, 2013 winter has arrived early in New York City. Light snow has just stopped dropping around 2 pm. The candlelight vigil in front of Saudi Arabia Mission to United Nations for the third time in a month went without any problem thanks to the brave New Yorkers who came out no matter what not deterred by cold weather.
An Open Letter to Jacky Gosse: Keep Your Head Up!
This past November Ethiopians in Saudi Arabia faced a “Green Terror” a terror inflicted on our people who were sheltered under Saudi Arabia Green Flag. Unknown numbers of Ethiopians were murdered and women were gang raped and many were viciously beaten. The world saw also mutilation of a dead Ethiopian young man covering his head with the Ethiopian Flag. The terror was against Ethiopians in Riyadh that forced them to go to deportation shelter for their own “safety”.
Similar crime is pending to unfold in Jeddah while the Arab media made headline news of

አንዱዓለም አራጌ ከእስር ቤት “እኔ እስሩ አልከበደኝም፤ በጣም ያሳዘነኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አለመቻላችሁ ነው” አለ


(ዘ-ሐበሻ) የ2005 ዓ.ም የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ምርጥ ተብሎ የተሰየመውና በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት የሚገኘው ወጣቱ ታጋይ አንዱዓለም አራጌ እስር ቤት ሊጠይቁት ለሄዱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች መልዕክት አስተላለፈ። በጣም ማዘኑንም ገለጸ።
Andualem Aragie
ዕድሜ ልክ እስራቱን ተቀብሎ እስር ቤት የሚገኘው አንዷለም አራጌ “ይቅርታ አልጠይቅም” በሚል እስካሁን በእስር ቤት እየማቀቀ ሲሆን “በእኔ መታሰር ብዙ ልትጠቀሙበት ስትችሉ አለመጠቀማችሁ ያሳዝነኛል:: እኔ አሁን በእስር ባለሁበት ሰዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ የነፃነት ትግሉን ወደ ፊት ለመግፋት አጋጣሚ ሊሆንላችሁ ቢችልም አልተጠቀማችሁበትም ” ሲል የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን መውቀሱን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
“እኔ መታሰሩና፤ በእስር ቤት እየደረሰብኝ ያለው ስቃይ አልከበደኝም። የከበደኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አለመቻላችሁ ነው። በኔ መታሰር መንግስት ብዙ ጫና ውስጥ እንዳለ ይታወቃል። በኔ መታሰር ብዙ ሥራ ልትሰሩበት፤ ትግሉን ወደፊት ልታስኬዱበት ስትሉ ይህን አላደረጋችሁም” ያለው አንዷለም አራጌ አሁንም የመንፈስ ጥንካሬው አብሮት እንዳለ በ እስር ቤት ካነጋገሩት ወገኖች መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።
አንዷለም አራጌ የፌደራሉ ማረሚያ ቤት የሚጠይቁህን ሰዎች ስም ዝርዝር አስመዝግብ ተብሎ ተጠይቆ የነበረ ሲሆን እርሱ ግን ማንም ሰው መጥቶ ሊጠይቀኝ መብቱ ነውና ስም ዝርዝር አውጥቼ አልሰጥም ሲል ፈቃደኛ አለመሆኑን ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መዘገቧ አይዘነጋም።
ምንጭ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/10722

ዶ/ር ቴዎድሮስ የሳዑዲውን ጉዳይ ለግል ዝና ማግኛ አውለኸዋል በሚል በጓዶቻቸው መወቀሳቸውን ለመንግስት ቅርብ የሆነ ሚዲያ ዘገበ


(ዘ-ሐበሻ) የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጥፋት ተከትሎ በፌስቡክ እና በትዊተር አማካኝነት ለሕዝብ መረጃ መስጠታቸው በኢሕአዴግ ባለስልጣናት ዘንድ እንዳልተወደደና እንደተተቹበት ለመንግስት ቅርብ እንደሆነ የሚነገርለይ ድሬ ቲዩብ የተባለው ድረ ገጽ ዘገበ። “የዶ/ር ቴዎድሮስ ግልጽና ተወዳጅ የዲፕሎማሲ ስልት በፖለቲካ ጓዶቻቸው ዘንድ እንዳስወቀሳቸው ተነገረ” ሲል ዘገባውን ያሰፈረው ድሬ ቲዩብ ዶ/ሩን በማሞካሸት ባቀረበው ዘገባው “አብዛኛው ፖለቲከኛጋ የማይታይ ቀለል ብሎ የሚያሸንፍ ስብዕና (Disarming Personality) የተላበሰና እንደሌሎቹ የተጠና ፖለቲካዊ ዲስኩር የማይደረድር፤ ካለበት የስልጣን ከፍታ አንጻር እሱን ማግኘት አይከብድም…በለውጥ ሀይል የተሞላና አብረውት ቢያወጉ የማይሰለች ተወዳጅ ነው የሚሉት ብዙዎች ናቸው የሚለው ዘገባ…አሁን አሁን ግን ይህ ባህሪ በፖለቲካ ጓዶቻቸው እንዳልተወደደላቸው ነው የሚነገረው፡፡” ሲል ገልጾታል።
tewedros adhanom with returnees
ድረ ገጹ ጨምሮም “በሶሺያል ሚዲያው ንቁ ተሳታፊ የሆኑት ዶ/ር ቴዎድሮስ በሳዑዲ ተመላሾች ዙሪያ በዋናው ሚዲያና በሶሺያል ሚዲያው ላይ በተደጋገሚ መታየታቸውና የነበራቸው ንቁ ተሳትፎ ከሁለት ሳምንታት በፊት በተደረገ አንድ ስብሰባ ላይ “ክስተቱን ለግል ዝና ማግኛነት አውለኸዋል” በሚል በፖለቲካ ጓዶቻቸው አስወቅሷቸዋል፡፡” ካለ በኋላ በተጨማሪም “በስብሰባው ወቅት ካስወቀሷቸው ጉዳዮች ሌላኛው፣ ለሳዑዲ ተመላሾች ማቋቋሚያ ባለሀብቶች የ7 ሚሊየን ብር እርዳታና ከተመላሾቹ የተወሰኑትንም

‘‘ፍርድ ሲዘገይ ሀገር እንደታሰረ መቆጠር አለበት’’ – ተማም አባቡልጉ (የሕግ ጠበቃ)

 
አቶ ተማም አባ ቡልጉ በአዲስ አበባ እየታተመ ከሚወጣው አዲስ ጉዳይ መጽሄት ቁጥር 128 ህዳር/2006 ዕትም ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ
temam ababulgu
አዲስ ጉዳይ፡ የሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ወደ ታህሳስ 3 ሲዛዋወር እንደ ጉዳዩ ዓቃቤነትዎ እንዲያውቁት ተደርገው ነበር?
ተማም፡ በፍጹም ለእኔ የተነገረኝ ነገር አልነበረም፡፡ ከእኔ ጋር አብሮ የሚሰራ ጠበቃ ፍርድ ቤት ድረስ ሄዶ ‘ጉዳዩ እንዴት ነው?’ ሲለኝ አይ እዚያው ነው ብዬ ሳረጋግጥለት ‘አረ ፍርድ ቤቱ ባዶ ነው’ የሚል ምላሽ ሰጠኝ፡፡ አንዳንድ ጠበቆች ጋር ስደውልም እከሌ የተባለ ጠበቃ እኮ ፍርድ ቤት በነበረበት ወቅት ከጽ/ቤት ተነግሮት ነበር አሉኝ፡፡ በዚህ ዓይነት መልኩ ነው ቀጠሮው መራዘሙን

Tuesday, December 10, 2013

አዳዲስ መረጃዎች በኢትዮጵያውያን የሳዑዲ አረቢያ ውሎ ዙሪያ (ከነብዩ ሲራክ)


ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ
ጅዳና ጀዛን – በጅዳ እና በጀዛን የሚገኙ የህግ እስረኞች በህግ ተይዘው ፍርድ ከተሰጣቸው በኋላ ለአመታት የሚጉላሉ እና በጥርጣሬ ተይዘው ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ዜጎች የድረሱልን ጥሪ ተበራክቷል። “ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሃገር ተመላሾች መሆኑ ብቻ ሳይሆን ድሮም ተረስተናል አሁንም ተረስተናል! ” እያሉ ነው! የሰሚ ያለህ!
ethiopian in Saudiጅዳ – ከጅዳ ወደ ሃገር ቤት የሚተመለሱ ዜጎች ቁጥር ወደ 60 ሽህ መጠጋቱን መረጃ ደርሶኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ከአሰሪዎች ጋር የትሰሩ ማናችሁም ዜጎች ያለማወላወል በሰላም ወደ ሃገር ግቡ በሚል ባሳለፍነው ያሰራጨው ጥብቅ ማሳሰቢያን ተከትሎ ወደ ሃገር ቤት ለመግባት የሚዘጋጁት ዜጎች ቁጥር ከፍ እያለ መጥቷል። ከዚሁ ጋር በተያያዥ “የሳውዲ ህግ ተለዋዋጭ ነው ፣ የምህረት አዋጁን ያራዝሙት ይሆናል!” በሚል ያልተጨበጠ ተስፋን የሰነቁ በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መዘናጋት አግባብነት እንደሌላውና ” ህገ ወጥ ” በሚል የተፈረጁ ከሃገር ይውጡ የሚለው ትዕዛዝ ከሳውዲው ንጉስ ቀጥተኛ የተላለፈ የማይታጠፍ ትዕዛዝ መሆኑን መራጃ ስለሆነ ዜጎች መዘናጋትን አስወግደው ያለማወላዎል ቁርጣቸውን አውቀው ይህን መልካም እድል ተጠቅመው ወደ ሃገር ቢገቡ ይሻላል ” በሚል የሳውዲና የመንግስታችን ተወካዮች በአጽንኦት በመምከር ላይ ናቸው!
ደማም – ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በደማም የሚገኙ ኢትዮጵያንን ወደ ሃገር መግባት ለማመቻቸት የሄዱት ልዑካን ከፊል

ግርማ ካሣ ቀልድ ጨምሯል!


ነጻነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ
የግርማ ካሣን ጽሑፎች አልፎ አልፎ አነባቸዋለሁ፡፡ ሀገር ወዳድ መሆኑን ይጠቁማሉ – ጽሑፎቹ፡፡ ታታሪ ሰው ይመስለኛል፤ በጥረቱና በሀገር ፍቅር ስሜቱ እወደዋለሁ፡፡ ሁልጊዜ ሳይታክት ይጽፋል፡፡ ሳይታክቱ የሚጽፉ ብፁዓንነት የሚበዛባቸው ቢሆን ዕድለኞች ግን ናቸው፡፡ ብዙዎቻችን እየደከመን መጻፍ ቀርቶ ማንበባችንንም እያቆምን በምንገኝበት ሰዓት አዘውትሮ መጻፍ መታደል ነው፡፡
አያ ግርማ ሰሞኑን የጻፋቸውን ሁለት ያህል መጣጥፎች አንብቤያለሁ፡፡ ሁለቱም ግንቦት ሰባትን ለመንቀፍ ብዕራዊ አንደበታቸውን ያሾሉ ናቸው፡፡ መነቃቀፍ በራሱ መጥፎ አይደለም፡፡ አግባብነትና እውነት ያለው መነቃቀፍ ወይም መወቃቀስ የዕድገት መሠረት በመሆኑ ሊጠላ አይገባውም፡፡ ነቀፌታንና ትችትን መፍራት ብልህነት አይደለም፡፡ ብሂሉ “ያልተቀጣ ሕጻን ሲቆጡት ያለቅሳል” እንደሚል አንድ በግለሰብም ይሁን በቡድን ደረጃ የሚገኝ አካል ጥፋት ካለው ያን ጥፋት በተጨባጭ መረጃና ከተገኘም ማስረጃ ነቅሰው ቢመክሩት መካሪውን “አንተን ብሎ መካሪ፤ ለራስህ ምን ታውቅና” በማለት ምክሩን ላለመቀበል መሞከር አስተዋይነት የሚጎድለው ጠያፍ ነገር ነው፡፡ አንድ ሰው ሌላው ቀርቶ ዕብድና ማይም ቢሆን እንኳን፣ ለሰው የሚያስላልፈው ገምቢ ሃሳብ አያጣም፡፡ ችግሩ መናናቅ ካልሆነ በስተቀር ወይም ጭፍን ጥላቻ ካላወረን አንዳችን ለአንዳችን ጥሩ መስተዋት ነን፡፡ ስንተቻች ግን የተደበቀ ሌላ አጀንዳ የምናራምድ ለመሆናችን ፍንጭ የሚሰጡ በቀጥታ ወይም በዐይነ ውሃችን የሚታወቁ ስስ ስሜቶች ከታዩብን ሚዛናዊነታችን ጥያቄ ውስጥ ይገባና ትዝብት ላይ ልንወድቅ እንችላለን፡፡ ጭፍን ፍቅርና ጭፍን ጥላቻ ሁለቱም በእኩል መንገድ ጎጂዎችና ጥቁር ጥላ የሚጥሉ ናቸው፡፡ መግባባት ሳይሆን መናቆርና ከንቱ መተቻቸት እንዲስፋፋ ያደርጋሉና ከነዚህ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡ ለገምቢ ምክርና አስተያየት ልቦቻችንን ቀና አድርገን ብንሳሳብ ተጠቃሚዎች እንሆናለን፡፡ አለበለዚያ የዱሮው ጥፋት በአዲስ መንፈስ ወደአዲስ ሰውነት ውስጥ እየተዛነቀ መስማማት ሳይኖር እንደስከዛሬው እየተቋሰልንና እየተዳማን እንኖራለን፡፡ ለማንኛውም በዚህ ረገድ ልቦናችንን ክፍት ብናደርግ ጥሩ ነው፡፡ መገፈታተር ይብቃንና ስሜት ለስሜት ለመናበብ እንጣር፤ አንጎዳበትም፡፡
ginbot 7የግርማን መጣጥፎች የምመለከተው እንግዲህ ከዚህ በላይ ከጠቆምኳቸው ሃሳቦች በመነሳት

“የኢትዮጵያ ሕዝብ የአጼ ምኒልክ ዕዳ አለበት” – የ80 ዓመቱ አቶ ከበደ ሙላት


 
minilik በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው እንቁ መጽሔት ላይ ታትሞ የወጣየ82 ዓመቱ አዛውንት አቶ ከበደ ሙላት ንጋት፤ የተወለዱት አዲስ አበባ ውስጥ ነው። ትምህርታቸውን በሐረር ልዑል ራስ መኮንን ት/ቤት የተከታተሉ ሲሆን፣ በመምህራን ማሠልጠኛ ማዕከል ገብተው የአስተማሪነት ሥልጠና ወስደዋል። በቀድሞው የጽሕፈት ሚኒስቴር መ/ቤት ከ1947 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በባሕር መዝገብ ዳይሬክተርነት፣ በዘውድ ም/ቤት ጸሐፊነትና በሌሎችም ዘርፎች አገልግለዋል። በኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማርያም አስተደደር ዘመን የኦምዱስማን (የዕንባ ጠባቂ) ተቋም አባል የነበሩት አቶ ከበደ፤ በቀድሞው የሠራተኛ አስተዳደር ኮሚሽን መ/ቤት የአስተዳደር ፍ/ቤት ዳኛም ነበሩ። በ1984 ዓ.ም መጨረሻ በራሳቸው ጥያቄ በጡረታ የተሰናበቱት ዕንግዳችን፤ ባለፉት 22 ዓመታት እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን ድረስ ያሉትን አገራዊና መንግሥታዊ መዛግብቶችን በማንበብ፣ በመመርመርና ታሪካዊ መጽሐፍ በማዘጋጀቱ ተግባር ላይ አትኩረዋል። ያዘጋጁት መጽሐፍም ባለ 550 ገጽ ሲሆን፤ የዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ መንግሥትን የሚመለከት፣ የንግሥተ-ነገሥታት ዘውዲቱንና የቀዳማዊ ዐፄ ኃ/ሥላሴን ጊዜያት ዋና ዋና ጉዳዮችን የሚዳስስና የሕትመትን ብርሃን ለማግኘት ስለኢትዮጵያ አንድነት ታሪክና ስለብልጽግናዋ የሚቆረቆሩ ባለሀብት ዜጎችን ድጋፍ የሚጠብቅ ነው። አቶ ከበደን የዳግማዊ ምኒልክን ሥርዓተ ቀብር 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ… ፍቃዱ ማኅተመወርቅ እና ሰሎሞን ለማ አነጋግረዋቸዋል።
kebede ዕንቁ፡- በታሪክ መጽሐፍዎ ረቂቅ ላይ ሦስት ኢትዮጵያን ያስጠሩ መሪዎች ስምና ተግባር መገለጹን ጠቁመውናል። ሦስቱ የሀገራችን መሪዎች እነማን ናቸው? ምኒልክስ ከሦስቱ በምን ይለያሉ?
አቶ ከበደ፡- ሦስቱ ነገሥታት ካሌብ፣ ቴዎድሮስና ዮሐንስ ናቸው። ዐፄ ካሌብ ከሰባ በላይ መርከቦችን ሠርቶና በሠራቸውም መርከቦች ብዙ ሠራዊት ይዞ ወደ አውሮፓ በመጓዝ ድል አድርጎ ስለመመለሱ በታሪክ የተጻፈለት ነው። ዐፄ ቴዎድሮስን ብንወስድ ለኢትዮጵያ ከፍተኛውን መስዋዕትነት የከፈሉና በዓለም ደረጃም እውቅናን ያተረፉ ናቸው። ከደርቡሾች ጋር ሲዋጉ መተማ (ጋላባት) ላይ የወደቁት የዐፄ ዮሐንስ ታሪክ አለ። የዮሐንስ መስዋዕትነት ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ክብር ስለሆነም ስመ-ጥሩ ናቸው።
እንግዲህ ከእነዚህ ዐፄ ምኒልክ የሚለዩት፤ ሥልጣኔ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ፣ የውጭ ቴክኖሎጂ ወደ ሀገራችን እንዲደርስ

“የምኒልክ ተግባር ዛሬ ያለንበትን ሀገር መዋቅር የሠራ በመሆኑ፤ የተዘፈነው ዘፈን ለክብራቸው ቢያንስ እንጂ የሚበዛ ሊሆን አይችልም” – ቴዲ አፍሮ (አዲስ ቃለምልልስ)


(እንቁ መጽሔት) ተወዳጁን ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሣሁንን በዚህ የመጽሔታችን ልዩ ዕትም፤ የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክን 100ኛ የሙት ዓመት… በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለመከበሩን ጉዳይ በተመለከተ ጥያቄዎች አቅርበንለታል። ቴዲም በምላሹ “በማንኛውም ሁኔታ ጥሩ የሠራን ሰው ማመስገን፣ ማክበር ጠቃሚ ባህል መሆኑን ተረድተን፤ በዚህ በኩል እስከዛሬ ያለውን ስሕተት ማረም አለብን” ብሏል። ሌሎች መሰል ሐሰብ አስተያቶችንም ሰንዝሯል። ሁሉንም ከቃለ-ምልልሱ ዝርዝር ይዘት ያገኙታል። መልካም ቆይታ!
ዕንቁ፡- የዳግማዊ ዐፄ ምንሊክ 100ኛ የሙት ዓመት በብሔራዊ ደረጃ አለመከበሩን እንዴት አየኸው?
Teddy afro minilikቴድዎሮስ፡- በቅድሚያ ከአከባበሩ አግባብነት ተነስተን ለይተን ልናስቀምጠው የሚገባ ነጥብ መኖር አለበት። ይከበራል የሚባለው ቀን የሞቱበት ይሁን፤ ሥርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመበት ወይስ ምኒሊክ በሠሯቸው አገራዊ ቁም ነገሮች ላይ ያአተኮረ ይሁን የሚለው ሀሳብ እራሱን የቻለ ውይይት የሚፈልግ ነው። እንዲህም ሆኖ ግን በግሌ የምኒልክ ማንነትም ይሁን ለኢትዮጵያ ያበረከቱት አስተዋፅኦ በብሔራዊ ደረጃ አለመከበሩ ያሳስበኛል።
ዕንቁ፡- በአንተ ግንዛቤ ከኢትዮጵያ ባሻገር ባለው ዓለም ብሔራዊ ኩራት የሆኑ ሰዎች ስለምንድነው የሚታሰቡት? አያይዘህም ምኒልክን በማክበር ሊገኝ ይችላል ብለህ የምታምንበትን ብሔራዊ ጥቅም ብትገልጽልን?
ቴድዎሮስ፡- ግለሰቦች እንዲታወሱ የሚደረግበትም ምክንያት፤ መሻሻልና መደገም ያለባቸው ጥሩ ታሪኮች ወደ አዲሱ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ስለሚፈለግ ነው። እነዛ ብሔራዊ ኩራት መሆን የቻሉ ሰዎች ሲታሰቡ ወይም የመልካም ስምና ተግባራቸው ማስታወሻ ዝግጅት ተደርጎ ክብራቸው እንዲገለጥ ሲደረግ፤ ሌሎች መልካም የሚሠሩ ሰዎችን ማፍራት የሚያስችል መነሣሣትን ይፈጥራል። በመሆኑም ነው ክብረ በዓሎች በታላላቅ ግለሰቦች ስም እየተሰየሙ፣ የእነሱም መልካምነት እየታሰበ የሚወሱበት አንድ ብሔራዊ ዝግጅት የሚከናወንበት ሥርዓት የሚያስፈልገው።
ዕንቁ፡- ዳግማዊ ምኒልክ ስለዛሬይቱ ኢትዮጵያ መፈጠር ሲሉ የገቡበትን ጦርነት እንዴት ነው የምትመለከተው?
ቴዎድሮስ፡- ምንጊዜም ሰዎች የሚበጃቸውን ነገር እስኪገነዘቡት ድረስ ያለመግባባቱ መጠን ይሰፋል። ያም ግጭት ሊፈጥር ይችላል። ይህም ደግሞ በእኛ ሀገር ሁኔታ ብቻ የተከሰተ ሳይሆን በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሆነም ነው። እንዲህም ሆኖ ግን ለምሳሌ ምኒልክ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ዘምተው ንጉሥ ጦናን ማረኩ። ከማረኳቸውም በኋላ እግራቸውን እያጠቡ ‹‹የእኛ አንድ አለመሆን፣ ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት አለመመሥረታችን፤ የጋራ ለሚሆነው ጠላታችን ጥቃት አሳልፎ የሚሰጠን አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ነው። በዚህ ምክንያት ነው ወደ አንተ ጦር ያዘመትኩት እንጂ ሥልጣንህን ለመቀማትና በአንተ ላይ ለመግነን… ፈልጌ አይደለም። ማእከላዊ መንግሥታችንን ማጠናከሩ ግን ሁላችንንም የሚጠቅመን ነው። አገራችንን፣ በሕላችንን፣ ታሪካችንን፣ ቋንቋችንን ጠብቀንና ድንበራችንን አስከብረን ለመኖር ይረዳናል›› ነበር ያሏቸው።
ለምንጊዜውም ነገሮችን በቀና ማየትና የጎደለውን ሞልቶ፣ ያለውን ጥሩ ነገር እንዳለ ይዞ መሄዱ፤ ለተሻለ ሀገራዊ ርምጃ ጠቃሚ ነው ብዬ አምናለሁ። ይህን የመሰለው አካሄድ ደግሞ በሌሎች አገሮች አልተሠራበትም የሚል ቅንጣት ዕምነትም የለኝም። ወቅቱ በረዳቸው መጠን የነበረውን የአንድነት ክፍተት ሞልተውና አመጣጥነው ማእከላዊ መንግሥቱን ከነበረው የግንዛቤ ማነስ ሁሉ… ቀድመው፤ በተቻለ መጠን በትህትና ዝቅ ብለው እግር በማጠብ ጭምር የነበረውን መጥፎ ሁኔታ መልክ ለማስያዝ ደክመዋል። ዛሬ ያለው ኢትዮጰያዊም ከተለያየ የኢትዮጵያ ብሔሮች ምንጭ ፈልቆ ይኸው በአንድነት ‹‹ኢትዮጵያዊያን ነን›› ለማለት ችሏል። ስለዚህ የምኒልክ ስም ብሔራዊ አክብሮት ማግኘት የሚገባው፣ በሕልውናችንም ላይ ከፍተኛ የሆነ ሚና ያለው፣ የተባበታተነውን ሰብስበው ያቆዩ በመሆናቸው ነው።
ዕንቁ፡- “በዐፄ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመሩት ሥልጣኔን የመከተል ጉዞዎች እንደጅምራቸው ቀጥለው ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ያደጉትን ሀገራት ጎራ ለመቀላቀል በቻለች ነበር” በማለት የሚቆጩ ወገኖች አሉ። አንተስ ምን ትላለህ?
ቴዎድሮስ፡- ያንን የሥልጣኔ ጅምር ከነበረው የኋላቀርነት ሁኔታ ጋር ሲመለከቱት ለመቀበል በጣም ከባድ ነበር። ለምሣሌ ‹‹ ስልክ ማነጋገር የሰይጣን ተግባር ነው…›› በማለት የተቃውሞ ሃሳባቸውን የሚሰነዝሩ ሰዎች ነበሩ። እንደዚህ ያለውን አመለካከት እና አስተሳሰብ አሸንፎ ለመሄድ ምኒልክ ብዙ ደክመዋል። ከዚህ ተነስተን የመሄዱ ጉዳይ በእሳቸው ተነሳሽነትና አስተማሪነት የተጀመረ ቢሆንም ቀዳማዊ ሀይለስላሴ በስልጣን ዘመናቸው ትምህርትን በማስፋፋት የተወሰነ ደረጃ ለማስኬድ መሞከራቸው የስልጣኔ

ከዋልድባ ነዋሪዎችን ማንሳት ተጀመረ


 
(ታሪክ ፈርሶ አዲስ ተመሰረተች የተባለችው የቆራሪት ከተማ)
(ታሪክ ፈርሶ አዲስ ተመሰረተች የተባለችው የቆራሪት ከተማ)

በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በዋልድባ ገዳም ላይ ለሚገነባው የስኳር ልማት ፕሮጀክት በመጀመሪያ ዙር 1800 አባወራዎች ከቦታቸው መነሳታቸውን አንድ አድርገን የተባለው የመረጃ መረብ ዘገበ። “ለተነሱ አርሶ አደሮቹ 127.5 ሚሊዮን ብር የካሳ ክፍያ ተሰጥቷል፡፡” ያለው ይኸው ድረገጽ ለእነዚህ ተነሺዎች ከወራት በፊት የገጠር ከተማ መልክ በመያዝ በተገነባችው የቆራሪት ከተማ ላይ የማስፈር ስራ ተከናውኗል፡፡” ካለ በኋላ “ለዚች ከተማ ምስረታ ምክንያት ደግሞ በዋልድባ ገዳም ላይ የሚሰራው የስኳር ልማት ፕሮጀክት መሆኑን” ዘግቧል።
“በአሁኑ ሰዓት ከቦታው የተነሱት 1800 ነዋሪዎች ከወልቃይት ወረዳ ፤ ከቃሌማ እና ፅምሪ ቀበሌ ይኖሩ የነበሩ አርሶ አደሮች ናቸው፡፡ መንግሥት እንደሚለው ለእነዚህ የልማት ተነሺዎች ለተነሱበት ቦታ በምትኩ የእርሻ ፤ የመኖሪያ ቤት ፤ ሙሉ የቤት እና

Sudan dilute Ethiopia, Toaster rescues Zambia


by ALEX ISABOKE on December 9, 2013
NAIROBI, Kenya, December 9 – Sudan are through to the semi finals of the GOtv Cecafa Senior Challenge Cup, after sending the Walia Ibex of Ethiopia home with a 2-0 win at Aga khan Stadium in Mombasa County on Sunday.
KINGATUA-ETHIOPIAThe surprise team of the tournament will play guest team Zambia after the Copper Bullets forced their way to the last four by edging out stubborn Burundi 4-3 on post-match spot kicks after both sides played out to a barren stalemate in the earlier match at the same venue.
Hosts Kenya and Tanzania who booked their semi slots on Saturday complete the last for line-up with the deciders for the December 12 finals being played on Tuesday at the Kenyatta Stadium in Machakos.
In the third quarterfinal, Salahadin Bargecho scored an own goal to give the Nile Crocodiles the opener, before Salah
Ibrahim netted the second to seal the victory.
Walia Ibex threatened in the early minutes of the game with Yousuf Yassin testing Sudan keeper

Monday, December 9, 2013

The man who taught Mandela to be a soldier


By Penny DaleBBC Africa,
Addis Ababa

mandelaaddisababa1962
General Tadesse Birru gave a pistol to Nelson Mandela as he returned to South Africa
In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare – including how to plant explosives before slipping quietly away into the night.
Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe – the armed wing of the African National Congress (ANC).
The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various

Health: ፍሬዬ ቦታውን ለቆ ወደ ውስጥ እየገባ ተቸግሬያለሁ


ከቅርብ አመታት ጀምሮ የቆለጥ ፍሬዬ ቢያንስ ለ1 ሰዓት ቦታውን ለቆ ወደ ውስጥ ማለትም ወደ ንፍፊቴ ከገባ በኋላ ከዚያ ወደ ትክክለኛው ቦታ ሲመለስ ያብጥና እጅግ በጣም ያመኛል፡፡ ራሴንም እስከመሳት ያደርሰኛል፡፡ ከዚያ ከ1-3 ቀን በኋላ ወደ ህክምና ስሄድ የሚሰጡኝ መፍትሄ የአባላዘር መድሃኒት ቢሆንም በፊት በፊት እጠቀም ነበር፤ በኋላ ግን ይህ በሽታ የአባላዘር እንዳልሆነና እኔም በሽታው የጀመረኝ በራሱ እንጂ ምንም አይነት የግብረ ስጋ ግንኙነት እንዳላደረኩኝ ስገልፅላቸው ሌላ መድሃኒት ይቀይሩልኛል፡፡ ይህ ምንም መፍትሄ አላመጣልኝም፡፡ በሽታው በስድስት ወር አንዳንዴም በዓመት እየተመላለሰብኝ አስቸግሮኛል፡፡ የሚድነውም በመድሃኒት ሳይሆን በአጋጣሚ ከብዙ ስቃይ በኋላ እየሆነ መጥቷል፡፡ አሁን አሁን በብልቴ ላይ የሚገኘው ደምስር ከነበረው እየወፈረ መጥቷል፡፡ ለጊዜው በሽታ ባይኖረውም ስጋት ፈጥሮብኛል፡፡ ይህንን ችግሬን ተረድታችሁ ምላሽ እንደምትሰጡኝ እተማመናለሁ፡፡ ዮናስ
ask your doctor
የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፡ ውድ ዮናስ እንደምን ከርመዋል? ለችግርዎ መፍትሄ እነሆ ብለናል፡፡ በብልት አካባቢ የተለያዩ ችግሮች ይፈጠራሉ፡፡ በዋናነት የአባላዘር በሽታዎች በብልት አካባቢ ችግር እንደሚፈጥሩ ቢታወቅም፣ ከአባላዘር በሽታ ውጪ የሆኑ የመራቢያ አካላትን ሊያበግኑ የሚችሉ በሽታዎች አሉ፡፡ አንዳንዴ ከመራቢያ አካላት አፈጣጠር ጉድለት የተነሳ ችግሮች ሊከሰቱ ሲችሉ፣ በአግባቡ የተፈጠረ የመራቢያ አካልም በአደጋና በተለያዩ ምክንያቶች ሊቃወስ ይችላል፡፡
ውድ ዮናስ ፡- እርስዎ የአባላዘር በሽታ ህክምና ሊያድንዎት አለመቻሉ እንዲሁም፣ የቆለጥዎ ወደ ንፍፊት አካባቢ እየገባ መጥፋት የሚያሳየው አንዳች የአፈጣተር ጉድለት በብልትዎ አካባቢ መኖሩ ነው፡፡ በሰው አፈጣጠር ሂደት ውስጥ በሆድ ዕቃና በቆለጥ ከረጢት መሀል በሆድ ዕቃና በቆለጥ ከረጢት መሀል አስቀድሞ ክፍተት ይኖራል፡፡ ይህ ክፍተት በራሱ የሚገጥም ሲሆን፣ ክፍተቱ ሳይገጥም ከቀረ ግን ቆለጥ ወደ ንፍፊት የሚገባበት፣ አንዳንዴም የሆድ ዕቃ አካላት ሾልከው ወደ ቆለጥ ከረጢት የሚገቡበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ እንዲህ ያለው የአካል አፈጣጠር ጉድለት በእርስዎ ላይ የታየውን አይነት ችግር፣ በህክምና (testicular torsion) ወይም የቆለጥ