Wednesday, March 5, 2014

የአፍሪካ መሪዎች ለምን ቶሎ ይሞታሉ? – በ6 ዓመት ውስጥ 10 የአፍሪካ መሪዎች ሞተዋል


 
meles zenawi
ቢቢሲ እንደጻፈው – አድማስ ሬዲዮ እንዳቀናበረው።
አንድ የአገር መሪ ፣ ገና በሥልጣን ላይ እያለ መሞቱ የተለመደ አይደለም። ነገር ግን ካለፈው 2008 ዓ.ም ወዲህ በዓለም ላይ 13 የአገር መሪዎች ገና ቢሯቸው እያሉ ሲሞቱ፣ ከዚያ ውስጥ 10 ያህሉ የአፍሪካ መሪዎች ናቸው። አፍሪካ ውስጥ መሪዎች ለምን ሥልጣን ላይ እያሉ ይሞታሉ?
በ 2012 ዓ.ም ብቻ አራት የአፍሪካ መሪዎች ቢሯቸው ውስጥ እያሉ ህይወታቸው አልፏል (የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የጋናው ፕሬዚዳንት፣ የማላዊ ፕሬዚዳንት፣ የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት) ። የመሪዎቹ ሞት ለጋዜጠኞች ደግሞ አዲስ የምርምር መንገድ ከፍቷል፣ – የአፍሪካ መሪዎች ለምን ቢሯቸው እንዳሉ ይሞታሉ?
“ሌሊት ስልክ ከተደወለልኝ፣ በቃ አንድ የአፍሪካ መሪ ሞቷል ማለት ነው ብዬ ማሰብ ጀምሬያለሁ” የሚለው የደቡብ አፍሪካው ዴይሊ ማቭሪክ ዜና አውታር ጋዜጠኛ ሲሞን ኤሊሰን ነው። እናም ይህን ጥያቄ ይዞ የትኛው መሪ በስንት ዓመቱ፣ በምን ምክንያት ሞተ? የሚለውን ምርምር ማድረጉን ቀጠለ።
ከ 2008 ወዲህ ብቻ 10 የአፍሪካ መሪዎች ሥልጣን ላይ እንዳሉ ህይወታቸው አልፏል። እነሱም ….
1- የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ፣ ዕድሜ 57 የሞት ምክንያት ድንገተኛ ኢንፌክሽን፣ የሞቱበት ወር ኦገስት 2012
2- የጋናው ፕሬዚዳንት ጆን አታ ሚልስ ፣ ዕድሜ 68፣ የሞት ምክንያት የጉሮሮ ካንሰር፣ የሞቱበት ወር ጁላይ 2012
3- የማላዊው ፕሬዚዳንት ቢንጉ ዋ ሙታሪካ ፣ ዕድሜ 78፣ የሞት ምክንያት ካርዲያክ አሬስት፣ የሞቱበት ወር ኤፕሪል 2012
4- የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ኤም ቢ ሳኒሃ ፣ ዕድሜ 64፣ የሞት ምክንያት የቆየ በሽታ፣ ለረዥም ጊዜ ታመው ቆይተው። የሞቱበት ወር ጃንዋሪ 2012
5- የሊቢያው ፕሬዚዳንት ሙ አመር ጋዳፊ ፣ ዕድሜ 69፣ የሞት ምክንያት በአማጺዎች ተገድለው፣ የሞቱበር ወር ኦክቶበር 2011
6- የናይጄሪያው ፕሬዚዳትን ኦማሩ ያር አዱአ፣ ዕድሜ 58፣ የሞት ምክንያት የኩላሊትና የልብ ህመም፣ የሞቱበት ወር ሜይ 2010
7- የጋቦን ፕሬዚዳንት ኦማር ቦንጎ፣ ዕድሜ 73፣ የሞት ምክንያት የልብ ድካም፣ የሞቱበት ወር ጁን 2009
8- የጊኒ ቢሳዎ ፕሬዚዳንት ጄ ቢ ቪየራ፣ ዕድሜ 69፣ የሞቱበት ምክንያት ተገድለው፣ የሞተበር ወር ማርች 2009
9- የጊኒ ፕሬዚዳንት ላንሳና ኮንቴ፣ ዕድሜ 74፣ የሞቱበት ምክንያት እስካሁን አልተነገረም፣ የሞቱበር ወር 2008፣
10- የዛምቢያ ፕሬዚዳንት ሌቪ ማዋናዋሳ፣ ዕድሜ 59፣ የሞቱበት ምክንያት ስትሮክ፣ የሞቱበት ወር 2008
እንግዲህ ከየትኛውም የዓለማችን አህጉር በአፍሪካ ተቀማጭ ፕሬዚዳንቶች በብዛት ህይወታቸው አልፏል። ከአፍሪካ ውጭ፣ በተመሳሳይ ወቅት ህይወታቸው ያለፈው የዓለም መሪዎች ሶስት ብቻ ሲሆኑ እነሱም የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ ታመው፣ የፖላንድ ፕሬዚዳንት ላች ካሲንኪ በአውሮፕላን አደጋ እና የባርባዶስ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ቶምሰን በካንሰር በሽታ ናቸው።
ከዝርዝሩ እንደሚታየው አፍሪካውያን መሪዎች ከሌሎቹ የዓለማችን አገሮች ይልቅ ዕድሜያቸው የገፋ ነው። ምናልባት አፍሪካውያን መሪዎቻቸው ሸምገል ያሉ እንዲሆኑ ይፈልጉ ይሆን? ሲል ይኸው ጋዜተኛ ሲሞን ኤሊሰን ይጠይቃል።
በዓለም ላይ ያሉ መሪዎችን ዕድሜ በአማካይ አውጥተን ስንመለከት፣ አፍሪካውያን ሸምገል ያሉ ሆነው ይገኛሉ። የዓለም መሪዎች በአህጉር ተከፋፍለው አማካይ ዕድሜያቸው ሲሰላ አፍሪካውያን መሪዎች በአማካይ ዕድሜያቸው 61፣ ኤዥያውያን 61፣ አውሮፓ 55፣ ሰሜን አሜሪካ 59፣ ደቡብ አሜሪካ 59፣ እንዲሁም አውስትራሊያ 58 ሆነው ተገኝተዋል።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ለረዥም ጊዜ በህይወት የመቆየት መጠን (ላይፍ ኤክስፔታንሲ) አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል። ይህም ከአህጉሪቱ የድህነት እና የበሽታ ታሪክ ጋር ይያያዛል። መሪዎች ሥልጣን ከያዙ በኋላ የተመቻቸ ኑሮ ቢኖራቸውም፣ ያደጉበት ህይወት በችግርና በሽታ የተጠቃ የድህነት ኑሮ ከሆነ እስከመጨረሻው ለረዥም ጊዜ የመቆየት ዕድላቸው ላይ ለውጥ እንደሚኖረው በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የዘር ጉዳይ ጥናት ሃላፊ ዶክተር ጆርጅ ሌሰን ይናገራሉ። ስለዚህም አፍሪካውያን መሪዎች በጊዜ ህይወታቸው ቢያልፍ፣ ከአህጉሪቱ ችግር ጋር የተያያዘ ምክንያት ሊኖረው ይችላል ማለት ነው።
በ2009 ዓ.ም በተደረገው ጥናት የአፍሪካውያን አማካይ በህይወት የመኖርያ ዕድሜ 75 ሲሆን፣ የየአሜሪካውያን 82፣ የአውሮፓውያን 81፣ የፓስፊክ አገሮች 80፣ የ ኤዥያውያን 77 ነው። ስለዚህ የአፍሪካ መሪዎች በጊዜ ሞት ቢያጠቃቸው ላይገርም ይችላል።
እንግዲህ የአፍሪካ መሪዎች በሥልጣን ላይ እያሉ የመሞታቸው ነገር አዲስ ባይሆንም፣ ብዙዎቹ በህይወት እያሉ ያስተካከሉት ነገር ከሌለ ድንገት ሲሞቱ ሥልጣኑን ለመያዝ የሚደረግ ሽኩቻ በህዝቡና በአገሪቱ ላይ ችግር ይፈጥራል .. ሲሉ ተንታኞቹ ይናገራሉ።
ምንጭ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13359

No comments:

Post a Comment