Sunday, September 21, 2014

ወጣትነት በአሁኗ ኢትዮጲያ


 
      ወጣትነት ማለት የአንዲት አገር ምሶሶ ወይም መሰረት መሆን የሚለውን ትርጉም ዕሰጠዋለው እንደኔ:: ባደጉት ሀገራት ውስጥ የአንድ ሀገር ሀፍት ወይም የኢኮኖሚ እድገት ሲለካ በዋናነት ወይም በመጀመሪያነት ኢሳብ ውስጥ የሚገባው ያላችውን እምቅ ሊሰራ የሚችል የወጣቱን ሀይል ማወቅ እና  ከዚያም በዋላ ወጣቱን እንዴት አድርገው ወደ ምርታማ አይል መንገድ ማሲያዝ እንደሚቻል በማወቅ ነው:: በምራባዊያን አለም ሞተር ለመኪና መንቀሳቀስ ከፍተኛውን አስተዋጾ እንደሚያደርግ ሁሉ ወጣቶችም ለሀገራችው ሞተር መሆናቸውን እናያለን:: ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል ብለን በምንጠይቅበት ጊዜ መልሱ በወቅቱ የነበሩት የሀገር አስተዳዳሪዎቸ እና ማሀበረሰቡ ለታዳጊው ትውልድ እና ለወጣቱ መሰጠት ያለበትን ትኩረት እና የአገር ፍቅር ሰጥተው ስላለፉ ነው:: ወደ ሀገራችን ኢትዮጲያ ስንመለስ ይሄ ነገር የተገላቢጦሽ ሆኖ እናገኘዋለን:: በይበልጥም ባለፉት 23 አመታት ውስጥ::
      ወጣትነት በኢትዮጲያ አስከፊና አሰቃቂ ሁኔታ ላይ የደረሰ ሲሆን በጣም የሚያሳዝነው ግን መንግስትም በዚው ጥፋት ላይ ከፍተኛውን ሚና መጫወቱ ነው:: እኔ በሙያዬ ፃሀፊ አይደለሁም ግን ወጣት እንደመሆኔ መጠን  በጓደኞቼ እና በአካባቤ የታዘብኩዋቸውን እና የሚያሳዝኑኝ ነገሮችን  እንደ ኢትዮጲያዊ በፃሁፍ መልክ ለአንባቢያን ላቅርብ ብዬ ነው ይሄን ፅሁፍ ለመፃፍ የተነሳሳሁት:: ከሁሉ አስቀድሜ ማየት የምፈልገው ጉዳይ ታዳጊ እፃናትን በተመለከት ነው:: ከአስራወቹ አመታት በፊት በአዲስ