Thursday, February 27, 2014

ታግደው የነበሩት መምህር ግርማ ወንድሙ ከፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል


(ዘ-ሐበሻ) መምህር ግርማ ወንድሙ በእስጢፋኖስ ቤ/ክ ከቀኖና ውጭ የማጥመቅ ሥራ እየሰሩ ነው በሚል መታገዳቸውን፤ የእገዳ ደብዳቤውን ጭምር በማያያዝ ዘ-ሐበሻ በወቅቱ መዘገቧ አይዘነጋም። ይህን እገዳ ተከትሎም መምህር ግርማ “እኔ አስማተኛ ወይም ጠንቋይ አይደለሁም” በሚል ለላይፍ መጽሔት የሰጡትን ቃለምልልስ በዘ-ሐበሻ ላይ አስነብበን ነበር። አሁን የደረሰን መረጃ ደግሞ የመምህር ግርማ ዜናን የሚቋጭ ይግሆናል።
የዘ-ሐበሻ ምንጮች በማስረጃ አስደግፈው እንዳደረሱን መረጃ ከሆነ መምህር ግርማ ወንድሙ በፓትሪያርክ አቡነ ማትያስ ፈቃድ በዓለም ዙሪያ እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የህሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ተፈቅዶላቸዋል። ከምንጮቻችን የደረሰን የተፈቀደበት ደብዳቤም የሚከተለው ነው።
Memher Girma
Memher Girma

ምንጭ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144

No comments:

Post a Comment