መምህር አማኑኤል ላይ እየደረሰ ስላለው ዛቻ የተጠየቁት የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሀብቶም “በስልክ መረጃ አልሰጥም” በማለት መምህር አማኑኤል ወንጀለኛ ነው የሚል ምላሽ ለፍኖተ ነፃነት ሰጥተዋል፡፡
ለመምህር አማኑኤል መንግስቱ በማዝገበ ብርሀን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ተመስገን ወ/ጊዮርጊስ ፊርማ በተሰጠው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ላይ እንደተጠቀሰው፡- የመንግስት ፖሊሲና ተግባሮች በተለያዩ አጋጣሚዎችና ድርጊት ማጥላላትና ሌሎችም እንዲያጥላሉ ተፅዕኖ ማሳደርና በተረጋጋና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየሰራ ያለውን ሰራተኛመብት ተረግጧል መብትህን ለምንድነው የማታስከብረው በማለት ሽብር የመንዛት ሙከራዎችን ማድረግ የሚሉ ሀይለቃሎች ይገኙበታል፡፡
የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል የማዝገበ ብርሀን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤት ሃላፊዎችን በስልክ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡
ምንጭ፣ http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/13177
No comments:
Post a Comment