Sunday, March 26, 2017

የሰቆቃ (የቶርቸር) ጥቃት እና ወያኔ!


ሰሞኑን የቀድሞ የአንድነት የፖለቲካ ፓርቲ (የእምነተ አሥተዳደር ቡድን) አመራርና ቀደም ሲል በወያኔ እስር
ቤቶች በታሰረበት ወቅት በነበረበት ኢሰብአዊ አያያዝ ለከባድ ሕመም በመዳረጉ አሁን ላይ ለከፍተኛ ሕክምና አሜሪካ
የሚገኘው አቶ ሀብታሙ አያሌው በቅርቡ ለአሜሪካ ድምፅ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል በሰጠው ቃለምልልስ ወያኔ
ሰብአዊና ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ) መብታቸውን በጠየቁ፣ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ጥረት ባደረጉ
ንጹሐን ዜጎች ላይ እየፈጸመው ያለውን ሰቆቃ (ቶርቸር) መግለጹ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጅ በመዘንጋት ይመስለኛል
ሀብታሙ በቃለ ምልልሱ ላይ ያልገለጻቸው ተጨማሪ አስከፊ የሆኑ የሰቆቃ ዓይነቶች በመኖራቸው ከሁለት ዓመት
ከመንፈቅ በፊት ቅሊንጦ እስር ቤት በነበርኩበት ጊዜ ከታሰርኩበት ክፍል ውስጥ ባገኘኋቸው ሁለት አንበሶች ማለትም
ስለሚወዳት ሀገሩና ሕዝቡ ሲል ለመግለጽ የሚከብድ ሰቆቃ ስለተፈጸመበት አበበ ካሴ እና በወያኔ አጠራር የጋምቤላ
ክልል ርእሰ መሥተዳድር ስለነበሩትና በወገናቸው በአኙዋኮች ላይ በወያኔ በተፈጸመው ጭፍጨፋ ምክንያት ወያኔን
ከድተው የፈጸመውን ጭፍጨፋ ለዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ስላጋለጡት አቶ ኦኬሎ አኳዬ ጀብድ “የቅሊንጦ አንበሶች!”
በሚል ርእስ ጽፌው ከነበረውን ጽፉፍ አሰቃቂ ሰቆቃ የተፈጸመበትን የአበበን ክፍል ነጥየ ባስነብባቹህ ያለውን
ሁኔታ በሚገባ ለመረዳት ያስችላቹሀልና በሚል አቀረብኩላቹህ፡፡
ታች አምና ከእስር ቤቱ እንደወጣሁ ይሄንን ጽሑፍ ለንባብ ላበቃው የቻልኩት በራሴ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን አበበ ካሴ
ማለትም ባለታሪኩ የተፈጸመበትን ኢሰብአዊ ግፍ ለሕዝብ እንዳደርስለት አደራ ብሎኝ ስለነበረም ነበር፡፡ ጽሑፉን
በማኅበራዊ የብዙኃን መገናኛ እንደለቀኩት የኢሳት ጋዜጠኛ ካሳሁን ይልማ ቃለ መጠይቅ አድርጎልኝ ነበር፡፡ ነገር
ግን በወቅቱ ግልጽ ባልሆነልኝ አሁን ግን ግልጽ በሆነልኝ ዕኩይና ጠባብ ምክንያቱ ቃለመጠይቁን በጽሑፉ ላይ
ታሪኩን ስለዳሰስኩት ሁለተኛው ሰው ማለትም በአቶ ኦኬሎ አኳዬ ላይ ብቻ እንዲያተኩር በማድረግ ዋነኛ የሰቆቃ
ሰለባ ስለሆነውና አስደናቂ ታሪኩ ሊነገርለት ይገባ ስለነበረው አበበ ካሴ እንዳነሣ ሳይፈቅድልኝ ቃለምልልሳችንን
ቋጨው፡፡

Wednesday, February 1, 2017

በአርበኞች ግንቦት 7 ስም የተከሰሱት እነ ንግስት ይርጋ በቀረበባቸው ክስ ላይ ያለቸውን ተቃውሞ አቀረቡ | መቃወሚያውን ይዘነዋል

በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት የተዘጋጀ
(ጥር 23/2009) አርበኞች ግንቦት ሰባት ከተባለ ሽብርተኛ ቡድን ተልእኮ በመቀበል እና የሽብር ቡድኑ አባል በመሆን በአማራ ክልል ውስጥ ከ2008 መጨረሻ እስከ 2009 መጀመሪያ ከ200 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ ማድረግ የሚል ክስ የቀረበባቸው እነ ንግስት ይርጋ ( ስድስት ሰዎች)፤ በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32[1] (ሀ) እና (ለ)፣ አንቀፅ 38 እና በፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 3 (4) እና (6) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ተብሎ ከአራት ወር የማእከላዊ ቆይታ በኋላ ከሶስት ሳምንት በፊት ክስ እንደተመሰረተባቸው የሚታወስ ነው።
በዛሬው ችሎት የሁሉም ተከሳሽ ጠበቆች በክሱ ላይ ያላቸውን መቃወሚያ ለችሎት በፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፤ ለአቃቤ ህግም የመቃወሚያው ቅጂ እንዲደርሰው ተደርጓል።
6ኛ ተከሳሽ የሆነው አቶ ያሬድ ግርማ ከ500 ገፅ በላይ የሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ እና ፊደል ላይ ያደረገው ጥናት ከማእከላዊ ወንጀል ምርመራ ማእከል እንዳልተመለሰለት ገልፆ፤ ከማእከላዊ ሲወጣ ወደ ማረሚያ ቤት እንደሚላክለት መርማሪዎች ነግረውት እንደነበር አስታውሶ እስካሁን ግን እንዳልተላከለት በመናገር እንዲሰጠው ትእዛዝ እንዲሰጥ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

5ኛ ተከሳሽ የሆነው በላይነህ አለምነህ፤ ፀረ ሽብር ህጉ በህገመንግስቱ አንቀፅ 20(መ) የተቀመጠውን “ተከሳሾች የቀረበባቸውን ማንኛውም ማስረጃ የመመልከት” እንዲሁም በህገመንግስቱ አንቀፅ 26(ለ) የተቀመጠውን “በስልክ እና በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች የሚደረጉ ግንኙነቶች አይደፈሩም” የሚለውን ድንጋጌ በመሻር እና ባጠቃላይ ህገ መንግስቱ ተጥሶ የወጣ አዋጅ እንደሆነ ተናግሮ ይህን ህገ መንግስት ለመጠበቅ በየተዋረድ ያሉ የመንግስት አካላት ሃላፊት ያለባቸው መሆኑን ተናግሯል። ዳኞችም ምን አይነት ማስረጃ እንዳልደረሰው 5ኛ ተከሳሽ በላይነህን ጠይቀውት የሰው ምስክር ማስረጃን በተመለከተ ምንም የደረሳቸው ማስረጃ እንደሌለ መልሷል። ዳኞችም የምስክሮችን ደህንነት መጠበቂያ እራሱን የቻለ መመሪያ እንዳለ ተናግረው፤ በሱ መሰረት ለምስክሮች ደህንነት ሲባል አድራሻቸውን እና ስማቸውን ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር አለመያያዙ ተገቢ እንደሆነ ተናግረዋል።
አቃቤ ህግ ተከሳሾች ባቀረቡት ተቃውሞ ላይ ያለውን አስተያየት ለመቀበል ቀጣይ ቀጠሮ ለየካቲት 7/2009 ተሰጥቷል።
በእነ ንግስት ይርጋ መዝገብ ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች የሚከተሉት ናቸው።
1ኛ ንግስት ይርጋ ተፈራ ( እድሜ 24, ሰሜን ጎንደር)
2ኛ አለምነህ ዋሴ ገ/ማርያም ( እድሜ 57, ሰሜን ጎንደር)
3ኛ ቴዎድሮስ ተላይ ቆሜ ( እድሜ 18, ሰሜን ጎንደር)
4ኛ አወቀ አባተ ገበየሁ ( እድሜ 31, አዲስ አበባ)
5ኛ በላይነህ አለምነህ አበጀ ( እድሜ 29, ባህር ዳር)
6ኛ ያሬድ ግርማ ሃይሌ ( እድሜ 46, አዲስ አበባ)
የክስ መቃወሚያዎቹን ዝርዝር ለማየት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጫኑ
ምንጭ : http://www.zehabesha.com/amharic/archives/71841

Friday, September 9, 2016

የአዲስ አበባ እንቅልፍ መንስዔው ምን ይሆን?

ይሄይስ አእምሮ (yiheyisaemro@gmail.com)
ውስጥ ውስጡን ከማጉረምረም ባለፈ አዲስ አበቤዎች የፍርሀት ቆፈናችንን አስወግደን በገጠራማዋ ኢትዮጵያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ለመቀላቀል እስካሁን ድፍረቱን አላገኘንም፡፡ ይህ ነገር  በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ አሳሳቢነቱ ደግሞ ለአዲስ አበባ ለራሷ እንጂ ለመላዋ ኢትዮጵያ እንዳልሆነ ወረድ ብዬ ለማስረዳት እሞክራለሁ፡፡  “ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ” ነው ነገሩ፡፡
አዲስ አበባ ለወትሮው የተቃውሞ ማዕከል ነበረች፡፡ እባብን ያዬ በልጥ በረዬ እንዲሉ ሆኖባት እንደሆነም አላውቅም ከ97 ምርጫ ወዲህ ግን ይህች ኩሩ የአፍሪካ መዲና ሕወሓትን በሰማንያ ያገባች የፍቅር እማውራ የሆነች ያህል በፀጥታ መዋጥን የመረጠች ይመስላል፡፡ እውነቱ ግን ሌላ ነው፡፡ በውስጧ ላለን እናውቀዋለን፡፡ የዜጎች ልቅሶና ዋይታ፣ የኑሮ ውድነትና የአፈናው መጠን ዜጎችን ከሰውነት ተራ አውጥቶ ወደ እንስሳነት እየለወጠ በመሆኑ የሕዝቡ ዝምታ ወያኔን ወዶና አፍቅሮ ሳይሆን በሆነ ደንቃራ ሳቢያ ፀጥ ረጭ ማለቱን እንደመረጠ መረዳት አይከብድም፡፡
File Photo
File Photo
ለመሆኑ ለምን ዝም አልን? ደንቃራው ምን ይሆን? የሚመስለኝን ልናገር፡፡
ደንቃራ አንድ – ከ97 የከሸፈ የወያኔ ምርጫ ወዲህ ሕወሓት በማን ምክር እንደሆነ አላውቅም የአዲስ አበባን የሕዝብ አሠፋፈር በከፍተኛ ደረጃ ለዋውጦታል፡፡ ከክፍለ ሀገር አዲስ አበባ ስትገቡ ትግራይ የገባችሁ እስኪመስላችሁ ድረስ ተጋሩ ወንድምና እህቶቻችን ከመቀሌና አካባቢዋ ዘመቻ በሚመስል መልክ ተጠራርገው ወደ አዲስ አበባና አካባቢዋ እንዲሠፍሩ የወያኔው ጉጅሌ ሣያደርግ አልቀረም፡፡ የትም ቦታ ስትሄዱ ሁለትም ሦስትም አሥርም ሃያም ሰዎች ሆነው ሲሄዱ የሚነጋገሩበት ቋንቋ አብዛኛውን ጊዜ ትግርኛ ነው –  ወትሮ በደጋግ ዘመናት ያልለመደበት ይህን መሰል ግምኛ ጠባይ ስለትግሬ ሲነገር ደማችሁ የሚንተከተክ (ዘረኛ) ሰዎች ታገሱኝ፤ እውነት ደምን ቀርቶ አጥንትን እንደምታፈላ ደግሞ አውቃለሁና በምለው ነገር ሀቅነት ማንም ቅንጣት ያህል እንዲጠራጠረኝ አልፈልግም፤ እውነትን ብትመር ብትጎመዝዝ እንዳለች መቀበል ነው፤ ይሉኝታና መሸፋፈን አስፈላጊ ሆኖ ቢገኝ እንኳን ተመክሮም ሆነ ተዘክሮ ዘመድ ለሚሆንህ ሰው እንጂ እንደበግ አጋድሞ ለሚያርድህ የትግሬ ወያኔ ዓይነቱ ደደብ ጭራቅ አይደለም፡፡ በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች ግዛቶች ብዙ ቀበሌዎች በትግርኛ ተናጋሪዎች እንደተሞሉ ለመረዳት የሥነ ሕዝብና የቤቶች ቆጠራ እስታትክቲክስ ሠራተኛ አያስፈልጋችሁም፡፡ በራሳችሁ ታውቃላችሁ፡፡ በነገራችን ላይ ትግሬዎች ኢትዮጵያን ለምን ሞሏት የሚል ቅሬታ የለኝም፤ ብዙዎቹ ከሕወሓት ጋር ያላቸው የክፋት ቁርኝት ነው የሚከነክነኝ፡፡ አንዳንድ ወንድሞች ታዲያን ይህን ዐይን ያወጣ “የወንድሞቻቸውን” ስህተት እየታዘቡ ሌላው ስለዚህ ስህተት ሲናገር መናደድ የለባቸውም – በአኮርባጅ እየተገረፈ ያለን ሕጻን “ዋ ታለቅስና! ዝም ብለህ ተገረፍ!” ብሎ እንደመቆጣትና ፈረንጆቹ `Adding an insult to injury” እንደሚሉት ነው – ድርብ በደል፡፡ ተጠቅመህም፣ እንዳልተጠቀምክ እንዲቆጠርልህ ፈልገህም እንዴት ሊሆን ይችላል? ብዙ ዕንቆቅልሽ … ብዙ ሞኝነት፡፡ በደል እንዲቆም ማድረግ ሲገባ “በደልህን ገሃድ አታውጣ” ብሎ ተበዳይ ላይ መፍረድ በሰማይም በምድርም ኩነኔ ነው፡፡ ከታላላቅ ምሁራን ጀምሮ ብዙ ብሶት ስላለኝ ነው …
የመንግሥት ሠራተኞች ባብዛኛው፣ ጦሩ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ፣ መከላከያንና ደኅንነትን፣ የውጭ ጉዳይንና ሌሎችንም የሚንስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም ንግዱንና የዕድርና የዕቁብ፣ የሰንበቴና የፅዋ ማኅበሩን የዜጎች ስብስብ የአመራር ቦታ ሣይቀር ሙሉ በሙሉ ወይም በአብዛኛው የያዙት ትግሬዎች መሆናቸውን መመስከር በተቃራኒ የቆመ ዘረኝነት አይመስለኝም፡፡ የዐዋጁን በጆሮ የመናገር ያህል ግልጽነት ነው፡፡ አንድ ወቅት ወደ ትግራይ ሄጄ ስመለስ በትግራይ ውስጥ የሚኖረው ትግሬ ሁለት ሚሊየን እንኳን እንደማይሆንና ቀሪው በመላዋ ኢትዮጵያ ተበትኖ በተቻለው መጠን እንደመዥገር ሀገሪቱን እየመጠመጠ እንደሆነ ከነባራዊው እውነት በመነሳት በጊዜው ገልጬ ነበር፡፡ ( በነገራችን ላይ ያን ትዝብት በድረ-ገፆች ከገለጥኩ ከጥቂት ሣምንታት በኋላ የኢሳት እንግዳ ሆና የቀረበችው ወ/ሮ ርስቴ የተባለች ጎንደሬ-ወልቃይቴዋ የቀድሞ የሕወሓት ቀጥሎም የኢሕዲን ተብዬው ታጋይ ስትናገርም ይህንኑ ነበር የተናገረችው፡፡ የኔን መጣጥፍ እንዳላነበበች እገምታለሁ፡፡ ግን እውነት እውነት በመሆኑ ሳይነጋገሩ ይግባቡበታልና እንዲያ ስትል እኔንም በጣም ገረመኝ፡፡ ለእውነቱ እርሷ ይበልጥ የቀረበች በመሆኗ የኔ የ2 ሚሊዮን ግርድፍ ግምት በዕውቀት ላይ በተደገፈ የርሷ መረጃ ጽድቅን አገኘ፡፡ በርግጥም ትግራይ ላይ ሰው ያለም አይመስልም፡፡ በወያኔ ተጠርተው ወደሌሎቹ ግዛች በመሄድ “ሥራ እየሠሩ” ነው፡፡)
ይህ የትግሬዎች – ማለትም የወያኔን ዕድሜ መርዘም የሚፈልጉና ለዚያ የሚዋደቁ የትግሬዎች ምልዓት ባለባት አዲስ አበባ ሕዝባዊ ተቃውሞን በቀላሉ መቀስቀስ ባይቻል አይገርምም፡፡ ሰው ለጥቅሙ ሲል የማያደርገው ነገር ስለሌለ እንኳንስ እነዚህ በዘረኝነትና በግል ጥቅም ታውረው ከትግራይ የመጡ ዜጎች ሌላው ጎሣ ሳይቀር ለነሱ ባሪያ በሆነበት ሁኔታ ከሕዝቡ ብዙ ነገር መጠበቅ በእስካሁኑ አካሄድ የሚቻል አልሆነም፡፡ ለምን ቢባል ትግሬው በዛ ማለት ስለላውም፣ ፀጥታውም፣ ምኑም ምናኑም በነሱ ቁጥጥር ሥር ስለሆነ ሰው ይፈራል – የሚገርማችሁ ዕብድና ሰካራም፣ ሴተኛ አዳሪና ቁራሌ እየሆኑ አሁን መንግሥት ከሆኑ በኋላም ሕዝቡን በስለላ ጥምድ አድርገው ይዘውታል – ሰሞኑን ደግሞ ብሶባቸዋል አሉ፡፡ በዚህ ምክንያት አዲስ አበቤ እርስ በርሱ አይተማመንም – አንዱ አንዱን ይጠራጠራል፤ ጥላውንም ማመን አቅቶታል፡፡ ጎመን በጤና ባዩ በዝቶ የእንስሳነት ኑሮ ሰፍኗል፡፡ ምሁር የለ ወታደር፣ ፖሊስ የለ ነጋዴ፣ ማይም የለ ዐዋቂ፣ ዲያቆን የለ ቀሲስ፣ ጳጳስ የለ ፓትርያርክ፣ ደረሣ የለ ኢማም፣ ሼህ የለ ቃዲ … ሁሉም ተያይዞ ነፈዝ ሆኖላችኋል፡፡ ስኬታማ ውድቀት ማለት እንዲህ ነው፤ ስንገርም!!
ደንቃራ ሁለት – ሕወሓት ብዙ ወጣቶችን በአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች አደራጅቶ የጥቅም ተጋሪ እንዲሆኑ አድርጓል፤ አእምሮ በጫጫበትና ስለሀገርና ወገን ማሰብ ዕርም በሆነበት ማኅበረሰብ ውስጥ ይህ ዓይነቱ ከፋፋይ ሥልት የራሱን አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር መገመት አለብን፡፡ ብዙ ሰዎች ስለሚያደርጉት ነገር ሳይሆን የሚያደርጉት ነገር በምን ያህል ፍጥነት ከበርቴ እንደሚያደርጋቸው ነው የሚያስቡት፡፡ ገንዘብ የሚገዛው ጭንቅላት ደግሞ ስለሀገር ቀርቶ ስለራሱም ማሰብ አይችልም፡፡ ሚሰቱንና ልጆቹን ሳይቀር ሸጦ በአቋራጭ መክበር የሚፈልግ ዜጋ በተበራከተበት የጨለማ ዘመን ውስጥ ብዙ መጠበቅ ያስቸግራል፡፡ አዎ፣ ብዙው ስታዩት ቀንም ሌትም፣ ቆሞም ተኝቶም የሚጨነቀውና የሚዋትተው ገንዘብ ስለማግኘት ነው – “የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው”፡፡ ይህ ዓይነቱ ለሥጋው ብቻ ያደረ ገልቱ ዜጋ ሀገሪቱን ብቻ ሳይሆን ከፍ ሲል እንዳልኩት ወንድሙንና እህቱንም ይሸጣል፡፡ እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እየበዙ ሲሄዱ ሀገር በባርነት ሥር እንዳለች የመቆየቷ ዕድል ከፍ ያለ ነው፡፡ መጸለይ ነው ጎበዝ! የተያዝነው የውጥርት ነው፡፡
ደንቃራ ሦስት – የ97ን ምርጫ ተከትሎ ሕወሓት አዲስ አበባ ላይ ያወረደው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ከሕዝቡ አእምሮ ገና አልወጣም፡፡ እንዲያውም ይባስ ብሎ የወያኔው ጉጅሌ ዐረመኔነቱን በየጊዜው እያደሰ መጥቶ ሰሞኑን ደግሞ በጭራሽ ሊታመን የማይችል ጭፍጨፋ በእስረኞች ላይ ፈጽሟል – ይህን መሰሉ በ“ሕግ ጥላ” ሥር ያለን ምስኪን ዜጋ በዚህ መንገድ መጨፍጨፍ ደግሞ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ይህ ጭፍጨፋ ሁለት መልእክት አለው ብዬ አስባለሁ- አንደኛው ሊያጠፋቸው የሚፈልጋቸውን የኅሊናና የደረቅ ወንጀል “የሕግ” እስረኞች ማጥፋት ሲሆን ሁለተኛው ሕዝቡን ማስፋራራትና ጭራቅ የመጣበት ያህል ቆጥሮ አንዳችም ተቃውሞ ሳያሳይ አርፎ እንዲቀመጥ ለማስጠንቀቅ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ ሁሉንም አየነው፤ ለየነው፡፡ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዕይታ ውስጥ ሆኖ ይህን ወንጀል በጠራራ ፀሐይ ሲሠራ ወያኔን አንድም አካል ዝምቡን እሽ ማለት ቀርቶ ከረር ያለ የቃላት ማስጠንቀቂያ እንኳን የሰጠው የለም –  ከተለመደው የ“ይህ ጉዳይ አሳስቦናል” ዲፕሎማሲያዊ የከንፈር ሽንገላ ውጪ ማለቴ ነው፡፡ ወያኔዎች “ምንም ብናደርግ የሚደርስላችሁ ስለሌለ ፀጥ ረጭ ብላችሁ ለኛ ተገዙ! አለበለዚያ አንድ ባንድ እንፈጃችኋለን፤ የዓለምን ፖለቲካ እንዳሻቸው የሚወስኑት ወገኖች እንደሆኑ ከኛ ጎን ናቸው” የሚል መልእክት ነው እያስተላለፉ ያሉት – ደግሞም እውነታቸውን ነው፡፡ እንዲህ ያለ ግፍ ሌላ ሀገር ቢሠራ ኖሮ ብዙ ዓለም አቀፋዊ ጩኸትና ውግዘት እንዲሁም እስከማዕቀብ የሚደርስ ከፍተኛ ግጭት ይፈጠር ነበር – ወያኔዎች ግን እስካሁን መንገዳቸው ሁሉ ቀኝ በቀኝ የሆነላቸው ይመስላል፡፡ ይህ እስር ቤቶችን በእሳት በማጋየት ከእሳት ለመዳን በደመነፍስ የሚሮጥን ወይም እሳቱ የተነሣው እስረኛን ለመፍጀት ሆን ተብሎ በወያኔ ሣይሆን በድንገተኛ አደጋ መስሎት እሳቱን ለማጥፋት የሚሞክርን እስረኛ ቀድሞ በተዘጋጀ አልሞ ተኳሽ ማስጨፍጨፍ የትም ሀገር ያልታዬ አዲስ የወያኔ ግኝት ለመሆኑ ማንም የማይክደው እውነታ ነው፡፡ ይህ ዐረመኔነታቸው ሕዝብን በፍርሀት ቆፈን ውስጥ እንዳለ እስከወዲያኛው እንዲቆይ ለማድረግ የታለመ እንጂ እስረኛን ለመግደል የሚከለክላቸው ምድራዊ ኃይል ኖሮ አይደለም፡፡ ይህን ፍርሀት ባፋጣኝ ካልገፈፍን ይበልጥ የምንጎዳው እኛው አዲስ አበቤዎች ነን፡፡ እነሱ እንደሆኑ እኛ ፈርተን እስከተቀመጥን ድረስ እየጨፈጨፉን ለዘላለሙ ይኖራሉ፡፡ ከነሱ የጭካኔ በትር የሚያድነን የውጭ ኃል እንደሌለ ደግሞ በሚገባ መረዳት ይኖርብናል፤ ግፋ ቢል ከንፈር ይመጡልን እንደሆነ እንጂ አንዲትም ወንጭፍ ሰንዝረው በኛ ላይ የሚተኩሱትን ወያኔዎች አደብ ግዙ አይሉልንም፡፡ ይህን ጠንቅቀን ማወቅ አለብን፡፡ እኛ ስንጠነክር ወደኛ ሊሳቡ ይችላሉ፤ ከተልፈሰፈስን ግን የወያኔዎች እንደሆኑ በዚያው ይቀራሉ፡፡ ግልጽ እኮ ነው፡፡ ጥሌ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” ብሎ ጨርሶታል፡፡
ደንቃራ አራት – የገጠሩ ሕዝብ በጎታውና በጉስጉሻው ለአንድ ሰሞን የሚያጋድደው(የሚሆነው) ጥራጥሬ አያጣም – እንደአብዛኛው ከተሜ ሙልጭ የወጣ ድሃ አይመስለኝም፡፡ እርግጥ ነው ተቃውሞውና ትግሉ ከተራዘመ ያም ያልቃል፡፡ ከተሜው በተለይም አዲስ አበቤው ግን ዛሬ ከሥራ ቢፈናቀል ቀጣዩ ቀን አሣር የሚሆንበትና ኑሮውን በብድር የሚገፋ ብዙ ጦም አዳሪ የመንግሥትና የግል ሠራተኛ የታጨቀባት ከተማ ናትና “ምን ላስጣ ከደጄ፣ ምን ልስጥ ለልጄ” በሚሉ ድሃ ዜጎች የተሞላች ናት፡፡ ሕዝብን አደሕይተው የሚገዙ ክፉ መንግሥታት የሚጠቀሙት እንግዲህ በዚህን ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሕዝቡ “ምን ልቅመስ?” እያለ ከጋራ ትግል ወደኋላ ሲያፈገፍግ ነው፡፡
ለሕዝባዊ ትግል ዝግጅት ያስፈልገዋል፤ ምክክር ያስፈልገዋል፤ ስምምነት ያስፈልገዋል፡፡ ያ እንዳይሆን ግን በሃሳብ መለያየት ይኖራል፤ በኑሮና በኢኮኖሚ አቅም መለያየት ይኖራል፤ የአሰባሳቢ ማጣትም ይኖራል…፡፡ ችግሮች ተደራራቢና ውስብስብም ናቸው፡፡ ይህን ሁሉ ችግር በጣጥሶ ለማለፍ ድፍረትና ጀግንነት ያስፈልጋል፡፡ ከራስ ማሰብ ባለፈ የትልቅ አእምሮ ባለቤት መሆንንና ዘመን ተሻጋሪ ታሪካዊ ሥራ ለመሥራት ዝግጁ ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል፡፡ ይህን ሚና ማን ይረከብ? አሳሳቢ ወቅታዊ ጥያቄ ይመስለኛል፡፡
ደንቃራ አምስት – በገጠሩ አካባቢ ያለው ሕዝብ ከፍተኛ ተመሳሳይነት (homogeneity) ስላለው ለመተማመንና ጥርጣሬን ለመቀነስ ብሎም በሂደት ለማስወገድ ትልቅ ዕድል አለው፡፡ በጎሣ ስብጥርም ሆነ በማኅበራዊ ትስስሩ ገጠሩ ከከተማው ይልቅ ይበልጥ እርስ በርስ ስለሚተዋወቅ ወኔው ካለው አንድን ነገር በጋራ አስቦ በጋራ ማድረግ አይቸግረውም – አሁን እያየነው ያለነውም ይህንን ነው፡፡ ከተማው ግን በተለይ አዲስ አበባ በየቀኑ በሚመጡላትና በሚመጡባት በርካታ ዜጎች የምትጥለቀለቅና በአንድ አዳር ከብረው በሚያድሩ ባለጊዜዎች የምትታመስ ከተማ በመሆኗና በገንዘብ ዝውውር ረገድም የት መጣ የማይባል እጅግ ብዙ ብር ሲረጭባት የሚውልና የሚያድር ከተማ ስለሆነች ሰው እርስ በርስ ለመተማመንና ልብ ለልብ ለመገናኘት ይቸግረዋል –  (ስለሆነም Heterogeneity አንዳንዴ አስቸጋሪ ነውና ማንኛውም ዕቅድና ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ይህን ችግር ታሳቢ አድርጎ መነሳት አለበት፡፡) በዚያ ላይ የወያኔ አጋፋሪዎች ሕዝብን በዘርና በጎሣ፣ በሃይማኖትና በጥቅማጥቅም በእጅጉ ከፋፍለውታልና ብሶቱ ሰማይ ቢነካም ለሕዝባዊ እምቢተኝነት ተቃውሞ ተጠራርቶ ለመነሣት አቀበት ሆኖብናል፡፡ ከውጪ እየገፋ የሚመጣ ኃይል ካልተገኘ በእስካሁኑ ሁኔታ ከአዲስ አበባ ብዙም መጠበቅ የሚቻል አልመሰለኝም፡፡ እንዲህ እንደሆነ ይቀራል ማለት እንዳልሆነ ግን በተለይ ወያኔዎች ሊረዱት ይገባል፡፡ የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡
መግቢያየ አካባቢ ወደጠቀስኩት ጉዳይ ልመለስና አዲስ አበቤዎች ሕዝባዊውን ሀገራዊ የእምቢተኝነት እንቅስቃሴ በሙሉ ንቃትና በስፋት ባለመሣተፋችን እንዴት ልንጎዳ እንደምንችል ልግለጽ፡፡
የአዲስ አበባ እስትንፋስ ወያኔ አይደለም፡፡ አዲስ አበባ የምትኖረው የገጠሩ ገበሬ ሲኖር ብቻ ነው፡፡ የገጠሩ ሕዝብ ሁሉን በሮቹን ቢዘጋ አዲስ አበባ ነፍሷን እንደምንም ብታውል አታሳድርም፡፡ ሁሉ ነገር የሚመጣው ከገጠር ነው – ከአየርና ከፀሐይ በስተቀር በአብዛኛው ሁሉም ነገር መነሻው ገጠር ነው፤ የፋብሪካ ግብኣቶች ሳይቀሩ የሚገኙት ከገበሬው ነው፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው ገዳይ የወሮበሎች መንግሥትና በሚሊዮን የሚቆጠር በላተኛ አፍ ያለው ተጨቋኝ የከተማ ነዋሪ እንጂ ጤፍና ስንዴ ወይም ምሥርና አተር ወይም የበሬ ቁርጥና የባቄላ አሹቅ አይደለም፡፡ ለቅንጦት የምናውለው ስኳርና ጨው ሳይቀር ከአዲስ አበባ ውጪ ነው የሚገኘው፡፡ ከሞላ ጎደል ሁሉም የምግብ ሸቀጦች ከገጠር ነው ወደ አዲስ አበባ የሚመጡት፡፡ የገፈርሳና የለገዳዲ ሕዝብ ቢያምጽና ውኃችንን አንሰጥም ቢል ራሱ – አያድርግብንና ለምሣሌ – አዲስ አበቤዎች በሕይወት የምንቆየው ግፋ ቢል ከሦስት እስከ ሰባት ቀን ቢሆን ነው፡፡ የኅልውናችን መሠረት ገጠሩ ነው፡፡ ከኛ ለኛ ምን አለን? ምንም፡፡ አልባሽ አጉራሻችን ገበሬው ነው፡፡ ካለ ገበሬው ምንም ማለት ነንና እርሱ በጥይት አረር በወያኔ እየተቆላ ዝምታችን የሚጠቁመው ወያኔን እንደመደገፍና ጠንከር ሲልም ጥይት እንደማቀበል ያህል ነው፡፡ ለምን ቢባል ወያኔ ለዱላ መግዣ የሚጠቀምበትን ግብርና ቀረጥ እንከፍላለንና፡፡ ዝምታችንም ተቃውሞን ብቻ ሣይሆን እንደድጋፍም ሊቆጠር ይችላልና፡፡
የጎጃምና የአድኣ ጤፍ፣ የቦረና በቆሎና የጨርጨር ሠንጋ፣ የጉራጌ ቆጮና የከፋና ሲዳሞ ወይም የወለጋና ጋሞጎፋ  ቡና፣ የሸኖ ቅቤና የአፋር-ዳሎል ጨው፣ የአዶላና ሻኪሶ ወርቅና የቤንሻንጉሉ የደን ዕጣን፣ የሙገሩ ስሚንቶና የጋምቤላው እምነ-በረድ፣… ወደ አዲስ አበባ ካልገባ በወያኔ ኢቢሲ በሚታየው እጅግ የተጋነነና የሀሰት የልማት ዜና ሆዳችንን ቀብትተን አንዲት ቀን ልናድር አንችልም፡፡
ስለዚህ አዲስ አበቤዎች የገጠሩን ሕዝብ የመቀላቀልና የሚደረገውን ሕዝባዊ የእምቢተኝነት ተቃውሞ ከዳር የማድረስ ኃላፊነትና ግዴታ አለብን፡፡ የኅልውናችን መሠረት የሆነው የገጠሩ ሕዝባችን ለሁላችንም መብት እየተዋደቀ እኛ በዝምታችን ብንጸና ፀፀቱ ለማያባራ የታሪክ ስብራት እንዳረጋለን፡፡ ይህን ውሸት ነው የምትል በአድራሻየ ተከራከረኝ፡፡ አዲስ አበባ ጌጧ ገጠሩ ነው፤ ካለገጠሩ ባዶና የባዶ ባዶ ነን፡፡ ይሄ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡
አዲስ አበባ ያለገጠሩ ሽባ መሆንዋን ሰሞኑን እየታዘብን ነው፡፡ የሁለት ሺህ ብሩ ጤፍ እስከሦስት ሺህ ብር እንደገባ እየሰማን ነው፤ ይህም የሆነው በኦሮሞ ሕዝባዊ ትግል ምክንያት የገበያና መንገድ መዝጋት እንቅስቃሴዎች ከመጀመራቸው ገና ከማለዳው ነው፡፡ ይህ ትግል በስፋት ቢቀጥል መቶ ሺህ ብርም ይዘህ – ቢኖርህ እንኳን ማለቴ ነው – አንዲት ጣሣ ጤፍ ላታገኝ የምትችልበት ጠማማ ዕድል ሊፈጠር ይችላል፡፡ ስድስት ሚሊየን ገደማ አፍ ይዘህ ተዝናንተህ መቀመጥ አትችልም – እርስ በርስህ ትበላላለህ፡፡ ኦሮሞና አማራ በተባበሩ ማግሥት ወያኔዎች ድራሻቸው እንደሚጠፋ የምንናገረው እንግዲህ ለዚህ ነው፡፡ የሽሮ ድንፋታ ከእሳት እስክትወጣ ነው ይባላል – የወያኔም ድንፋታ ኦሮሞና አማራ እጅ ለእጅ ተያይዘው ከባርነት ለመውጣት እስኪወስኑ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ አለቀ!!!
ሕዝቡ የከተማ የገጠር ብሎ ሳይፎካከር ሕዝባዊ ተቃውሞውን በአንድ ጀምበር ካደረገ ወያኔም በአንድ ጀምበር ይወገዳል – በዚያው ተመሳሳይ ጀምበር፡፡ ወያኔዎች እርግጥ ነው በገንዘብ ዕጥረት አይወገዱም – ለሚሊዮኖች ዓመታት የሚሆናቸውን ከበቂ በላይ የሆነ ሀብትና ንብረት ዘርፈው አሽሽተዋልና፡፡ በጥይት ዕጥረትም አይወገዱም – በበቂ ሁኔታ አጠራቅመዋልና፡፡ ግን ግን የኅልውና አማራጭ የሚያጣ ሕዝብ እንደንብ በአንዴ ሆ ብሎ ከሠፈረባቸው አጋዚም በሉት መከላከያና ደኅንነት አቅሙ ውሱን ነውና በእግር አውጪኝ የትሚናውን እንደሚፈረጥጥ ግልጽ ነው፡፡ የሮማንያ ሕዝብ የሞተው ሞቶ የተረፈው ተርፎ ሀገሩን ከኒኮላይ ቻውቸስኮ አምባገነን አገዛዝ ነፃ ያወጣው ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ባደረገው ሕዝባዊ ተጋድሎ ነው፡፡ በተናጠል ከሄድን ግን የትም አንደርስም፡፡ ለተራዘመ ትግል ደግሞ የሚያመች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዳራ የለንም፡፡ ስለዚህ ምርጫችን ሁለት ብቻ ነው፡፡ አንድም በነካካነው የቆሰለ የቤታችን (ዐውሬ) አነር እየተዘነጠሉ መኖር፣ አለዚያም በተናጠልም በቡድንም የነካካነውን ክፉኛ የቆሰለ አነር ገድለን ለሁላችንም የሚጠቅም አዲስ ሥርዓት መትከል፡፡ ለዚህ ደግሞ መሸዋወዱና “የነ እገሌ ትግል ይቅደም፣ የነ እገሌ ትግል ደግሞ ይቀጥል” በሚል የሞኛሞኞች የትግል ሥልት መጃጃል የለብንም፡፡ ከሆነ በአንዴ ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ ወያኔን “ባጠፋን ይቅር በለን፣ የድፍረታችን ምንጭ ልማታችንና ሕዝባዊ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ሥርዓታችን ባመጡብን ጥጋብ የተወለደው አቅል አሳች ስካር ነው” ብለን ሕወሓትን ይቅርታ ጠይቀን የከፋ የከረፋውን የውስጥ ቅኝ አገዛዝና የአፓርታይድ ጉዞ ማስቀጠል ነው፡፡ ከዚህ ውጪ “ገመቹ ይቅመሳትና ደስታ በተራው ይታገላል፣ የለም – ሐጎስ እስኪነሣ አሸምቀን እንጠብቅ፣ አሃ፣ ደቻሳ የቀመሳትን ዱላ ስንሻው ካልቀመሳት እንዴት በጋራ እንታገላለን? …” እየተባባሉ ወንዝ በማያሻግርና ካለፈ ተሞክሮ አንዳችም መማማር በሌለበት የድንቁርና አካሄድ ከቀጠልን እመኑኝ የትም አንደርስም – ለነገሩ ይሄ የምለው ነገር የአደባባይ ምሥጢር እንጂ “እመኑኝ አትመኑኝ” የሚያስብል አዲስ ግኝት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡ ግን ግን ካለፈ ታሪክና ከአሁን የግል ጠባሳችን የማንማረው ምን ቢዞርብን ወይም ወያኔ ምን ዓይነት አፍዝ አደንግዝ ቢያስደግምብን ይሆን?
ኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጥረህ ከአንዱ ወይ ከሌላው ጎሣ ያልተቀላቀልህ የለህምና በዚህ በወያኔ ዘራሽ የጎሠኝነት ልምሻ የተኮደኮድክ ሁሉ በአሁኑ ወቅት ሙሉ የመንቂያ ጊዜ ላይ ደርሰሃልና በቶሎ ንቃ፡፡ የጋራ ጠላትህንም ባፋጣኝ ለይና በጋራ ሆነህ ባላንጣህን ተፋለም፡፡ በቃ፡፡ ሌላ መፍትሔ የለም፡፡
በውጪ ያላችሁትም በቻላችሁት ሁሉ በትግሉ ተሣተፉ፡፡ ማጨብጨብና መሰለፍ፣ በየተወሰነ ጊዜ ጠላትን በሰላማዊ ሰልፍ ማውገዝም ብቻውን በቂ አይደለምና የትግል ሥልትህን ለውጥ፤ ሲበቃ በቃ ነውና የትግል ዘዴህን ባለመለወጥ ትርፍ በማያመጣ መጯጯህ ጊዜህን በከንቱ አታባክን፡፡ ኢትዮጵያውያን ዳያስጶራዎች በአካልም፣ በመንፈስም፣ በገንዘብም፣ በዕውቀትም፣ …. በሁሉም ረገድ በትግሉ ተሣተፉ፡፡ “ሩቅ ሆነው በርገር እየቆመጡ ድሃውን ያገር ቤት ሰው ጃዝ ይላሉ” ከሚለው ወደ እውነት የቀረበ አቃቂር ለመዳን ሲሞቅ በማንኪያ ሲቀዘቅዝ በእጅ እንደሚባለው ሣይሆን በማንኛውም አቅጣጫ በንቃት መሣተፍ አለባችሁ – የመጨረሻው የጥፋት ወይም የትንሣዔ ዘመን የቀረበ ይመስለኛል – አሁንም ከሁለቱ አንዱን የመምረጡ ግዴታ የኛው ነው፡፡ የነፃነትን ዋጋ ሁሉም ይረዳ፡፡ በነፃ የሚገኝ ነገር ርካሽ ነው የሚባለው አንዳንዴ ትክክል ነው፡፡ ወዳገር ቤት ገብታችሁ በአመራርም ሆነ በውጊያ መሣተፍ ካለባችሁም በሩቅ ሆኖ በንዴት ከመብገንና ከመጨስ ባመቻችሁ ቀዳዳ ገብታችሁ ትግሉን ተቀላቀሉ፡፡ እርግጥ ነው – መናገር ቀላል ነው – ይህን የኔን ጨምሮ፡፡
ምንጭ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/65600

Friday, May 22, 2015

“በመመካከር ከራሷ ጋር የታረቀች አገር ጥንስስ እኛው ውስጥ እንፍጠር” -አርበኞች ግንቦት 7 -

አርበኞች ግንቦት 7 በመርህ ላይ በተመሠረተ ትብብር ወያኔን በጋራ ታግሎ ማሸነፍ እና በየደረጃው የሚገኝ የመንግሥት ስልጣን ነፃ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒን በሆነ የሕዝብ ምርጫ ብቻ የሚያዝበት የፓለቲካ ሥርዓት መገንባት የአርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ተልዕኮ ነው። በዚህም መሠረት አርበኞች ግንቦት 7፣ በተግባራዊ እንቅስቃሴ ላይ ከሚገኙት ከትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ ከጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ፣ ከቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ እና ከአማራ ዴሞክራሲ ኃይል ንቅናቄ ጋር በመርህ ላይ በተመሠረተ ትብብር በጋራ ለመታገል የሚያስችለውን ስምምነት ላይ እየደረሰ ነው። 
ginbot 7

ይህ የትብብር ጥረት ብዙ ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጠንካራ ድጋፍ ይሻል። ህወሓትን ከስልጣን የማባረር ኃላፊነት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ኃላፊነት ነው። ይህ ትልቅ ኃላፊነት በአንድ ወይም በጥቂት ድርጅቶች ላይ መጣል የለበትም። ይህ ትብብር ይህንን የጋራ ኃላፊነትን በጋራ ለመወጣት የተደረገ በዓይነቱ አዲስ የሆነ ተግባራዊ ትብብር ነው። ህወሓት በትግራይ ውስጥ መቶ በመቶ ተቀባይነት ያለው አስመስሎ ፕሮፖጋንዳ ሲነዛ ቆይቷል። ህወሓት፣ የትግራይና የአማራ ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያዩ፤ የትግራይ ሕዝብ ራሱን ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጥሎ እንዲያይ የረዥም ግዜ እቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ ነው። ይህን እኩይ ሴራ ማክሸፍ የምንችለው በፀረ-ወያኔ ተግባራዊ ትግል በጋራ ስንቆም ነው። ይህ ትብብር ለአገራችን አንድነትና ዘላቂ ሰላም ወሳኝ የሆነው በፀረ ህወሓት አቋሙ የጠነከረ የትግራይ ሕዝብ እንዲኖር ወሳኝ ሚና ይኖረናል ብለን እናምናለን። በአሁኑ ሰዓት የህወሓት አገዛዝ የቆመው ዘረኛ በሆነ መንገድ ባደራጀው ጦር፣ በስለላ ድርጅቱ እና ኃያላን መንግሥታት ለጥቅማቸው ሲሉ በሚያደርጉለት ሁለተናዊ ድጋፍ ነው። እነዚህ ህወሓትን ደግፈው የያዙ ኃይሎች ጠባቸው ከመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መሆኑን በተግባር የምናሳያቸው ተግባርን መሠረት ያደረገ ጠንካራ ኅብረት ፈጥረን ስንገኝ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ነባራዊ ማኅበራዊ ሀቅ ምክንያት ከፓለቲካ አመለካከት ይልቅ በወል ማንነት ላይ የተመሠረቱ ድርጅቶች የሚበዙበት ሆኗል። የኢትዮጵያን ችግር ለመፍታት ሁለቱን አመለካከቶች መሠረት አድርገው በተደራጁ ድርጅቶች መካከል ትብብር መፍጠር ወሳኝ ነው። 
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከላይ በአጭሩ በተዘረዘሩት ምክንያቶች እየተፈጠረ ያለው ትብብር የኢትዮጵያን የፓለቲካ መልካምድር ወደተሻለ ሁኔታ ለመቀየር የራሱ አስተዋጽዖ ይኖረዋል የሚል እምነት አለው። በዚህም ምክንያት መጠናቀቅ የሚገባቸው ነገሮች ተጠናቀው ትብብሩ በይፋ እንዲመሠረት የበኩሉን ጥረት ያደርጋል። ከላይ በተዘረዘሩት ምክንያቶች ሳቢያ የትብብር አድማሳችን ከዚህም መስፋት አለበት ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም፣ በተለያዩ ምክንያቶች ለጊዜው የትብብር ማዕቀፍ ውስጥ ያልገቡ የፓለቲካ ድርጅቶች ወደ ትብብሩ እንዲመጡ፤ ለሀገራችን እና ለሕዝብ በጋራ መሥራት በምንችላቸው ጉዳዮች ላይ እንድመክር ጥሪውን ያስተላልፋል። በመመካከር ህወሓትን ማስወገድ ብቻ ሳይሆን ለሁላችን የሚበጅ የተሻለ ሥርዓት በአገራችን ላይ እንዲመሠረት መሠረት መጣል እንችላለን ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። ስለሆነም እንነጋገር፤ ለሁላችን የሚበጀንን መንገድ በጋራ እንፈልግ፤ የህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝን በጋራ እንታገል፤ ከራሷ ጋር የታረቀች አገር ጥንስስ እኛው ውስጥ እንፍጠር ይላል። ለውጤታማ ትግል እንተባበር! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!! - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/41535

Friday, February 27, 2015

የመለስ ትሩፋቶች ደራሲ ኤርሚያስ ለገሰ ለዲያቆን ዳንኤል ክብረት የጻፈው ግልጽ ደብዳቤ

ከአንድ ሰአት በላይ የፈጀውን ጥናታዊ ጵሁፍህን ሰማሁት። ሰምቼ ስጨርስ ደነገጥኩ። ከራሴም ጋር ለሰአታት ሙግት ገጠምኩ ። ኢህአዴግን ለቅቄ የወጣሁት ልቤ የፈቀደውን በነጳነት ለመናገር ነውና የማውቀውን እና የሚሰማኝን መናገር እንዳለብኝ ተሰማኝ ። ርግጥ በሐይማኖት ጉዳዬች ላይ መናገር ከባድ እንደሆነና ዋጋ እንደሚያስከፍል ጠንቅቄ አውቃለሁ ። በሌላ በኩል የሚያውቁትን አለመግለጵም የፀፀት ዋጋ አለው። በመሆኑም ባለመናገሬ ከሚሰማኝ ሙግት መናገሩን ስለመረጥኩ የሚከተለውን አጭር አስተያየት ለመስጠት ተገደድኩ። 1• ያቀረብከውን መረጃዎች እንዴት እንዳሰባሰብካቸው የተገለፀ ነገር የለም። በተለይም በድህረና ቅድመ ምርጫ 97 ባሉት ሶስት አመታት( ከኃላም ከፊትም) ያቀረብካቸውን መረጃዎች ምንጭ ማወቅ እፈልጋለሁ ። ይህን ጥያቄ የማነሳበት መሰረታዊ ምክንያቶች ስላሉኝ ነው።

daniel kibret

 1•1• በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2001 አ• ም• ኢሕአዴግ ለሕዝቡ ይዞለት የመጣው እቅድ ” በአክራሪነት ” ስም ሀይማኖቶችን ማዳከም ነበር። ይህንንም ለማቀጣጠል እንዲረዳው በኢህአዴግ ቢሮ፣ በኮሙዩኒኬሽን ጵ/ ቤት፣ ፌደራል ጉዳዬች እና ፌደራል ፓሊስ መረጃ እንዲሰባሰቡ ተደረገ። የእስልምና ጉዳዬች ላይ ዝርዝር ጥናቱን እንዲሰራ የቤትስራ የተሰጠው ሽመልስ ከማል ነበር። ዛሬ አንተ ካቀረብክልን ውስጥ ግማሹ የቃላት ለውጥ እንኳን ሳይደረግለት በሽመልስ ከማል ጥናታዊ ፅሁፍ የቀረበ ነበር። በወቅቱ እጅግ ከመደንገጤ የተነሳ ሽመልስ እንዴት እንዲህ አይነት ጥናት እንደሰራ ለማወቅ ከጀርባው መጓዝ ነበረብኝ ። መጓዜ ያልጠበኩትን ውጤት አመጣ። ሽመልስ በእስልምና ላይ ከፍተኛ ጥላቻ የያዘው በቤተሰቡ ውስጥ በተፈጠረው ምስቅልቅል እድገት መሆኑን ተገነዘብኩ። አባቱ በአንድ ወቅት የመስኪድ አስተዳደር ነበሩ። በኃላ የሳውዲ ጉዞ አድርገው ሲመለሱ አስተዳደሩን በመነጠቃቸው ከሀይማኖቱ በተቃራኒ ተሰለፋ ። ” ከመካ መዲና ደርሶ መልስ” የሚል መጵሀፍ አሳትመው ክርስትና ተነሱ። ስማቸውም ወደ ሀይለየሱስ ተቀየረ። ባስታወቀው እርምጃ ቤታቸው ተመሰቃቀለ።ወንድማማች እና እህታማቾች የሚጠሩበት የአባት ስም እስከ መለያየት ደረሰ። ባጭሩ የሽመልስ ፀረ -እስላም የመሆን ምንጩ ይሄ ነው። በመሆኑም በሽመልስ ሲቀርቡ የነበሩ ዳታዎችና ትንታኔዎች እንደወረዱ ከአንተ ሲቀርቡ ስሰማ የመረጃ ምንጭህን ተጠራጠርኩ። በተለይ

Monday, February 23, 2015

የወያኔ ሚኒስተር ከ30 እስከ 40% የግንባታ ወጭ እንደሚዘረፍ አሳወቁ


1619564_780737625344507_8633815854074255488_n
የኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና፣ ከቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑን አምነዋል።
የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት በባቡር መስመር ግንባታ 2.3 ኪሜ የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚልዮን በር ኪሳራ ደርሷል። የአደጋ መከላከያ ብረቶች የተሰሩት ከወጣላቸው የጥራት ደረጃ በሶስት እጅ ያነሱ ሆነው በመገኘታቸው ጉዳዩ ለቦርድ ሰብሳቢው ዶ/ር አርከበ እቁባይ ቢቀርብም ምላሺ ሰይሰጠው በመቅረቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገባ ማወቅ አለመቻሉን ገልጿል።
የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ምላሺ የሰጡት ሚኒስትር መኩሪያ ሃይሌ ፣ ችግሩ የተፈጠረው ለምርጫው ሲባል የባቡሩ ግንባታ እንደ ትልቅ የምርጫ ማሰመኛ በመያዙ ነው ።
የግንባታ ኢንዱስትሪው ከሚያወጣው ወጪ ከ30 እስከ 60 በመቶ የሚሆነው በሙስና ይባክናል ሲሉም ሚኒስትሩ አክለዋል። እንደዚያም ሆኖ በቅርቡ የተመረቀ የአዲስ አበባ መለስተኛ የባቡር ግንባታ፣ አገልግሎት ከመጀመሩ ከወዲሁ በርካታ የመፈራረስ ችግሮች እያጋጠሙት ነው። ለፖለቲካ ፍጆታና ለፕሮፖጋንዳ ሲባል ቶሎ ቶሎ እንዲሰራ ከማድረግ ዉጭ እነ አቶ አርከበ እቁባይ የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት ያላስገቡ ሲሆን፣ አስፈላጊ የጥንቃቄ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በዋናነት የባቡ ሃኢዱ ከተማዋን ለሁለት የከፈለ ሲሆን ከሃዲዱ በስተቀኝ እና በስተግራ ያሉ ነዋሪዎች ለመገናኘት እጅግ በጣም ብዙ ረቀት ለመጓዝ ተገደዋል።
ምንጭ: http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/17401

Friday, November 14, 2014

ፌደራል ፖሊሶች ለሚፈጽሟቸው ግድያዎች ተጠያቂው ማን ነው? (ከዳዊት ሰለሞን)

dawit
ከዳዊት ሰለሞን
ይህ ጥያቄ በቀጥታ በመንግስት ትዕዛዝ የተፈጸሙ ግድያዎችን አይመለከትም፡፡እንደውም በፓርላማ ከቀረበው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ‹‹በግዳጅ ላይ ያለ የመንግስት ታጣቂ ለሚፈጽመው ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆን ››የሚሞግት ነው፡፡
ፓርላማው 446 ለ 1 የሚመራ በመሆኑም ገዢው ፓርቲ የፈለገውን አዋጅ የማውጣት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡በዚህ ገጽ ግን ለማንሳት የወደድኩት ታጣቂዎች ከስራ ገበታቸው ውጪ እየፈጸሟቸው የሚገኙ ግድያዎች ሀላፊ ማን ይሆናል የሚለውን ነው፡፡
ንፋስ ስልክ አካባቢ የመንግስት የሰላም አስከባሪ አባል የነበረ አንድ መቶ አለቃ ጎረቤቶቹን በ35 የክላሽ ጥይት መግደሉና ህጻናቱን ያለ ወላጅ ማስቀረቱ አይዘነጋም፡፡
መቶ አለቃው ከታሰረ በኋላ በልዩ እንክብካቤ ተይዞ ወላጆቻቸውን ባጡ ህጻናት ላይ ይዘት እንደነበርና በኋላም አመለጠ ተባለ፡፡መቶ አለቃው መጨረሻ ላይ ስለመያዙ ተነገረ፡፡
ባህርዳር የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አንዘነጋውም፡፡አፍቅሪያታለሁ ያለ ፌደራል ፖሊስ የ18 ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሞተ የሚል ወሬ ተናፈሰ፡፡
ቂርቆስ መንደር በምትገኝ የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር እንዲሁ የእኔ የሚላትን ሴተኛ አዳሪ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ በማግኘቱ ፌደራሉ በሁለት ጥይት ደረቷን መትቶ ለህልፈት ዳረጋት ፣ከሴትየዋ ጋር የነበረው ጎልማሳም እግሩን በጥይት ለመቆረጥ በቅቷል፡፡
ይህ ፎቶ ግራፍም በተመሳሳይ መንገድ በፌደራል ፖሊስ ህይወቱን በግፍ ስለ ተነጠቀ ወጣት የሚጮህ ነው፡፡
ጅማን በእንባ፣በድንጋጤና በተቃውሞ የሞላ ክስተት የተስተናገደው በፌደራል ፖሊስ ነው፡፡በምሽት ሰው ቤት ሰብሮ የገባው ፖሊሱ አንዲት አይነ ስውር

Friday, November 7, 2014

ሰሞኑን በጋምቤላ በተከስተው ግጭት 60 የሞቱ ; 36 የተሰደዱ; 4 የደረሱበት ያልታወቀና 23 የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ዝርዝር

የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ሰመጉ ባወጣው 132ኛ ልዩ መግለጫ በክልሉ በመንገሽና ጎደሬ ወረዳዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተገደሉ የ60 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል። ዝርዝሩን ይመልከቱ
ምንጭ ፣ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35980
gambela
gambela 2





gambela 3

Saturday, November 1, 2014

Eight Ethiopian Air Force Pilots Defected In October

A total of eight Ethiopian Air Force pilots have defected this month, according to a senior Eritrean official.
Ethiopian MiG-23
Ethiopian MiG-23

The official didn’t specify if the pilots defected to Eritrea, or if they managed to flee the country with their aircrafts, though it is highly likely they did in both cases.
The defections come as reports indicate the Ethiopian Air Force is in shambles, and that the TPLF oligarchs are “disgusted” by their poor performances.
Ethiopia is no stranger to high-profile air force defections. Last year, four Ethiopian helicopter pilots and a MiG-23 pilot defected to Eritrea.
The names of the helicopter pilots are Cap. Aklilu Mezene, Cap. Tilahun Tufa, Cap. Getu Worku and Cap. Biniam Gizaw, while the name of the MiG-23 pilot is Daniel Yeshewas.
source: http://www.zehabesha.com/eight-ethiopian-air-force-pilots-defected-in-october/

Tuesday, October 28, 2014

Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).

FOR IMMEDIATE RELEASE
MEMORANDUM
TO: The United Nations Security Council Sanctions Committee
FROM: Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.
DATE: October 27, 2014
SUBJECT: Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy expresses its high regards to The United Nations Security Counciland would like to use this opportunity and bring to the attention its reservations regarding some references made about it in SEMG report of October 13, 2014.

1. The SEMG report states that “Ginbot 7 is a banned opposition group”. We would like to call the attention of the International Community to the infamous “Anti-Terrorism Proclamation” promulgated by the TPLF/EPRDF regime of Ethiopia with the aim of stifling political dissent. The dictatorial regime has used this proclamation as an instrument to label and criminalize Ginbot 7, as well as other political opposition organizations, human rights advocacy groups, civil society, journalists and bloggers inside and outside of Ethiopia.

Sunday, October 12, 2014

Ana Gomez faults the British on Andargachew Tsige case

Member of the European Parliament Ana Gomez blamed London for being soft on Ethiopia and, in particular, for the extradition of British national Andargachew Tsege.Ana-Gomez-European-parliament_thumb
The MP made the remarks in an EU Parliament subcommittee hearing that focused on Andargachew Tsege, who was second-in-command of the rebel group Ginbot 7. The man was detained on June 23 at Sana’a international airport, Yemen, when he was transiting to Eritrea, and subsequently extradited to Ethiopia.
Andargachew’s detention became public knowledge after a week, when his group issued a statement. Another week passed before Ethiopia confirmedthat the Yemenis extradited him, while the Yemeni are silent to date.
During the two weeks of information black-out the British claimed that they were “press[ing] the Yemeni authorities at senior levels to establish [Andargachew's] whereabouts”.
It was on July 8, the same day that Ethiopia confirmed to have the man in custody, Britain’s Foreign and Commonwealth Office confirmed the extradition.
Ms. Gomez, however, is of the opinion that the British had been feigning ignorance in those

Saturday, October 4, 2014

4.4 billion people around the world still don’t have Internet. Here’s where they live

An exhaustive new study by McKinsey & Company (really, it’s 120 pages long) about the barriers to Internet adoption around the world illuminates a rather surprising reality: 4.4 billion people scattered across the globe, including 3.2 billion living in only 20 countries, still aren’t connected to the Internet.
no internet ethiopia
The sheer number of people unconnected in some countries is staggering. India is home to nearly a quarter of the world’s offline population; China houses more than 730 million; Indonesia 210 million; Bangladesh almost 150 million; and Brazil nearly 100 million. Even in the United States, 50 million people don’t use the Internet (though, as my colleague Caitlin Dewey points out, many of those who are offline in the United States are offline by choice).
But adjusting for size, and instead looking at the percentage of people in certain countries that still aren’t connected to Internet, shows that quite a few places have very little internet penetration at all. In Myanmar, 99.5 percent of the population is offline; in Ethiopia, almost 98 percent; in Tanzania, more than 95 percent; and in the Democratic

Sunday, September 21, 2014

ወጣትነት በአሁኗ ኢትዮጲያ


 
      ወጣትነት ማለት የአንዲት አገር ምሶሶ ወይም መሰረት መሆን የሚለውን ትርጉም ዕሰጠዋለው እንደኔ:: ባደጉት ሀገራት ውስጥ የአንድ ሀገር ሀፍት ወይም የኢኮኖሚ እድገት ሲለካ በዋናነት ወይም በመጀመሪያነት ኢሳብ ውስጥ የሚገባው ያላችውን እምቅ ሊሰራ የሚችል የወጣቱን ሀይል ማወቅ እና  ከዚያም በዋላ ወጣቱን እንዴት አድርገው ወደ ምርታማ አይል መንገድ ማሲያዝ እንደሚቻል በማወቅ ነው:: በምራባዊያን አለም ሞተር ለመኪና መንቀሳቀስ ከፍተኛውን አስተዋጾ እንደሚያደርግ ሁሉ ወጣቶችም ለሀገራችው ሞተር መሆናቸውን እናያለን:: ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል ብለን በምንጠይቅበት ጊዜ መልሱ በወቅቱ የነበሩት የሀገር አስተዳዳሪዎቸ እና ማሀበረሰቡ ለታዳጊው ትውልድ እና ለወጣቱ መሰጠት ያለበትን ትኩረት እና የአገር ፍቅር ሰጥተው ስላለፉ ነው:: ወደ ሀገራችን ኢትዮጲያ ስንመለስ ይሄ ነገር የተገላቢጦሽ ሆኖ እናገኘዋለን:: በይበልጥም ባለፉት 23 አመታት ውስጥ::
      ወጣትነት በኢትዮጲያ አስከፊና አሰቃቂ ሁኔታ ላይ የደረሰ ሲሆን በጣም የሚያሳዝነው ግን መንግስትም በዚው ጥፋት ላይ ከፍተኛውን ሚና መጫወቱ ነው:: እኔ በሙያዬ ፃሀፊ አይደለሁም ግን ወጣት እንደመሆኔ መጠን  በጓደኞቼ እና በአካባቤ የታዘብኩዋቸውን እና የሚያሳዝኑኝ ነገሮችን  እንደ ኢትዮጲያዊ በፃሁፍ መልክ ለአንባቢያን ላቅርብ ብዬ ነው ይሄን ፅሁፍ ለመፃፍ የተነሳሳሁት:: ከሁሉ አስቀድሜ ማየት የምፈልገው ጉዳይ ታዳጊ እፃናትን በተመለከት ነው:: ከአስራወቹ አመታት በፊት በአዲስ

Wednesday, August 20, 2014

Andargachew Tsige Family Called on the British Government

August 19, 2014

The family of a British citizen kidnapped and rendered to Ethiopia in June has called on the British government to secure his release as soon as possible.

Reprieve – Andargachew ‘Andy’ Tsege, a father of three from London, was travelling to Eritrea in June this year when he was seized during a stopover in Yemen. Two weeks later, Ethiopian officials admitted to the UK government that Mr Tsege was in their custody.
British consular staff were denied access to Mr Tsege over 50 days after his initial capture, and his family still do not know where is being held. Last month, Prime Minister Hailemariam Desalegn dismissed concerns about Mr Tsege’s concerns and whereabouts.The UK government and Andargachew Tsege
Mr Tsege, who is a prominent member of an Ethiopian opposition group, faces a death sentence imposed in absentia, and his arrest comes amid a crackdown on political activists and journalists ahead of elections in Ethiopia next year. In a heavily-edited video aired recently on Ethiopian state TV, Mr Tsege appeared thin and exhausted, and was presented as having ‘confessed’ to various charges.
Torture in prisons in Ethiopia is common; a 2013 Human Rights Watch report on the notorious

Saturday, July 26, 2014

Ginbot 7: Movement for Justice, Freedom and Democracy Special Statement and Call for Action – We Are All Andargachew Tsege!!!

         

Ginbot 7: Movement for Justice, Freedom and Democracy

Special Statement and Call for Action

We Are All Andargachew Tsege!!! ( pdf )

The long and bitter struggle has now transitioned to a new chapter designated as “We are all Andargchew Tsege”. This communiqué briefly describes what this new chapter is about and what it constitutes. The tasks outlined here are not to be read and set aside rather a series of concrete plans to be put into action.
What does it mean to be Andargachew Tsege? Andargachew Tsege is our leader who stands for justice, freedom, democracy and equality, who has been paying and still paying the immeasurable sacrifices that the struggle requires. To be like Andargachew Tsege means to be humble but determined, patient but persistent, visionary and wise and always ready for action. What it means to be an Andargachew Tsege is to be that person ready to take the necessary measures to get rid of the brutal regime systematically destroying our country. To become an Andargachew Tsege means to be the salvation for our beloved country and our generation.
One of the reasons why the minority regime of the Tigrai People’s Liberation Front (TPLF) has targeted Andargachew Tsege is because he is a leader who has managed to establish close ties between the armed Oromo, Afar, Ogaden, Gambella and other ethnic based organizations and Ginbot 7, our movement in a manner that renders ineffective the tribal junta’s propaganda. Above all what

Monday, July 7, 2014

Ethiopia: Fears for Safety of Returned Opposition Leader

 
July 7, 2014
(London) – An exiled Ethiopian opposition leader unlawfully deported by Yemen back to Ethiopia is at risk of mistreatment including torture. Andargachew Tsige is secretary-general of Ginbot 7, a banned Ethiopian opposition organization, and was convicted and sentenced to death in absentia in separate trials in Ethiopia in 2009 and 2012.

The current whereabouts of Andargachew, a British national, is unknown, raising concerns for his safety. The Ethiopian government should take all necessary steps to ensure Andargachew’s safety and his right to a fair trial. Many individuals arrested in politically related cases in Ethiopia are

Amnesty International: Ethiopian activist Andargachew Tsige at risk of torture

July 6, 2014
Amnesty International

URGENT ACTION ETHIOPIAN ACTIVIST AT RISK OF TORTURE

Amnesty International on Andargachew TsigeAndargachew Tsige, an Ethiopian political activist in exile, appears to have been arrested in transit in Yemen on 24 June and forcibly returned to Ethiopia. He is at risk of torture and other ill-treatment. Andargachew Tsige is a British national of Ethiopian origin and Secretary-General of Ginbot 7, an outlawed Ethiopian opposition group. He disappeared on 24 June at Sana’a airport in Yemen, while in transit between the United Arab Emirates and Eritrea. Although no official statements have been released by the Yemeni or Ethiopian authorities about his current whereabouts, human rights activists in Yemen told Amnesty International that he was forcibly returned to Ethiopia the same day he landed after being detained at the Sana’a airport.
He is at high risk of torture and other ill-treatment in Ethiopia, where political detainees are frequently tortured in order to extract information and confessions. His incommunicado detention in

Tuesday, July 1, 2014

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት

Wednesday, June 25, 2014

በሀዋሳ በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ዛሬም የረሀብ አድማ ላይ ናቸው!! በሀዋሳ ሰ.መ.ጉ እስረኞችን እንዳይጎበኝ ተከለከለ – የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 15 ቀን 2006ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ‹‹ፍትህን ተነፍገን ትግላችን አይቆምም ››በማለት ዛሬም ለ4ኛ ቀን በርሀብ አድማ ላይ ናቸው፡፡አባላቱ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቅዳሜ እለት ጀምሮ በረሀብ አድማ ላይ ሲሆኑ በትላንትናው እለት ሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው በኢ/ፌ/ዲ/ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 27(1-ሀ)32/1-ሀ/እና 257 ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ በሚል የአዋሳ ከተማ ከፍተኛ ዐ/ሕግ ክስ ተመስርቶባቸው የዋስትና መብታቸው ተነፍጎ በእስር እንዲቆዩና ዓቃቤ ህግ ምስክሮቹን ለሰኔ 20 ቀን 2006 እንዲያሰማ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በማስተላለፉ ወደ እስር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡
በተያያዘም ዜና ሰ.መ.ጉ በሃዋሳ ከተማ በእስር ላይ የሚገኙትን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላትን ሁኔታ ለመመልከት ወደ ወደ ሃዋሳ እስር ቤቶች ያመሩት የሰብዓዊ መብት ጉባዔ ሀላፊዎች እስረኞቹን ለማግኘት እንደማይችሉና ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ትዕዛዝ በመተላለፉ ምክንያት ታሳሪዎቹን ማግኘት እንዳልተቻለና የጣቢያ ሀላፊዎቹን ለማናገር የተደረገውም ጥረት እንዳልተሳካ አስረድተዋል፡፡

10450753_657204294364508_6267425299544943631_n
10448208_657204214364516_9050720156707149922_n

ምንጭ፣ http://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/15021